Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኢሜሬቶች በቴምር ምርት ላይ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኢሜሬቶች በቴምር ምርት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ከተባበሩት አረብ ኢሜሬቶች የከሊፋ ኢንተርናሽናል ቴምር አዋርድና የግብርና ኢኖቬሽን ዋና…

ፈጣን የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት ጂኦፊዚካል ጥናት ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ፈጣን የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት ጂኦፊዚካል ጥናት ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል፡፡ ለ5 ዓመት የሚተገበረውን ፕሮጀክት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከዴንማርክ መንግስት ጋር በመተባበር ነው ይፋ…

ለደጃዝማች ኩምሳ ሞረዳ ቤተ-መንግስት የመልሶ ማልማት ሥራ ሊከናወን ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደጃዝማች ኩምሳ ሞረዳ ቤተ-መንግስት የጥገና እና የመልሶ ማልማት ሥራን ለማከናወን የውል ስምምነት መፈረሙን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረ/ፕ/ር) በዚህ ወቅት÷…

የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሥርጭትን ለመቆጣጠር ርብርብ እንዲደረግ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጋምቤላ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ ሥርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የጋራ ርብርብ እንዲደረግ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ፡፡ የክልሉ ጤና ቢሮ ከ ሲ ዲ ሲ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የኤች አይ ቪ ኤድስ…

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለ293 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጠረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ293 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ አስታውቋል። የቢሮው ሃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ እንዳሉት÷ በበጀት ዓመቱ ከ350 ሺህ በላይ…

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በባህል፣ ኪነ ጥበብና ስፖርት ዘርፍ በጋራ ለመስራት ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በኢትዮጵያ ከሩስያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን ጋር በባህል፣ ኪነ ጥበብ እና ስፖርት ዘርፍ በጋራ መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል። በውይይቱ ኢትዮጵያ የብዝሃ ባህል ባለቤት እና ታሪካዊ ሀገር…

መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) መንግስት በፈጠራ እና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ የትምህርት፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ እንዲሁም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴሮች ከአፍሪካ ብሬይንስ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት…

ከ52 ሺህ በላይ የአዕምሯዊ የፈጠራ ውጤቶች መመዝገባቸው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ52 ሺህ በላይ የአዕምሯዊ የፈጠራ ውጤቶችን መመዝገቡን የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ ዓለም አቀፍ የአዕምሯዊ ንብረት ቀን ለ25ኛ ጊዜ "ሙዚቃና አዕምሯዊ ንብረት" በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ሥነ-ሥርዓቶች በመከበር ላይ…

የመደመር ትውልድ ቤተ-መጻሕፍት ግንባታን በቅርቡ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር ትውልድ መጽሐፍ ሽያጭ ገቢ እየተገነባ የሚገኘው የድሬዳዋ አሥተዳደር የመደመር ትውልድ ቤተ-መጻሕፍት ግንባታን በሦስት ወራት ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ቤተ-መጻሕፍቱ…

ኢትዮጵያ በ3ኛው የአፍሪካ-ኢራን ኢኮኖሚያዊ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በቴህራን እየተካሄደ በሚገኘው 3ኛው የአፍሪካ-ኢራን ኢኮኖሚያዊ ትብብር ጉባኤ እና በኢራን ዓለም አቀፍ ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈች ነው፡፡ ጉባኤው በዋናነት በኢራን እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን የኢንዱስትሪ፣ የንግድና…