Browsing Category
ስፓርት
አትሌት ለሜቻ ግርማ በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ሩጫ ክብረ ወሰን በመስበር አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ለሜቻ ግርማ በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ሩጫ ውድድር የዓለም ክብረወሰን በመስበር አሸንፏል፡፡
አትሌት ለሜቻ ርቀቱን በ7 ደቂቃ 52 ሰከንድ 11 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ክብረ ወሰን በመስበር…
የሀድያ ሆሳዕና እና የአዳማ ከተማ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ከተማ 3ለ 3 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ጥሩ ፉክክር በታየበት በዚህ ጨዋታ አዳማ ከተማ 3 ለ 0 እየመራ ቢቆይም ሀድያ ሆሳዕና ነጥብ መጋራት ችሏል።
በጨዋታው…
የስድስት ሀገራት አትሌቶችን የሚያሳትፈው የአስመራ ማራቶን የፊታችን እሑድ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያን ጨምሮ የስድስት ሀገራት አትሌቶችን የሚያሳትፈው የአስመራ ማራቶን በመጪው እሑድ እንደሚካሄድ የኤርትራ ባህልና ስፖርት ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
የኤርትራ ባህልና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ዘመዴ ተክሌ ÷በውድድሩ መርሐ ግብር የወንዶች…
ሪያል ማድሪድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ በቤሊንግሃም ዝውውር ሲስማሙ ሊዮኔል ሜሲ ወደ አሜሪካ ሊያቀና ነው
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሪያል ማድሪድ እንግሊዛዊውን የቦሩሲያ ዶርትመንድ አማካይ ጁዲ ቤሊንግሃምን ለማስፈረም መስማማቱ ተሰምቷል።
ሎስብላንኮዎች አማካዩን ለማስፈረም 113 ሚሊየን ፓውንድ የሚከፍሉ ሲሆን፥ ተጫዋቹም ስድስት አመታት የኮንትራት ውል እንደሚፈርም…
ካሪም ቤንዜማ የሳውዲ አረቢያውን ክለብ ለመቀላቀል ተስማማ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፈረንሳዊው የሪያል ማድሪድ አጥቂ ካሪም ቤንዜማ የሳውዲ አረቢያውን ክለብ አል ኢቲሃደን ለመቀላቀል ተስማማ፡፡
ቢቢሲ ማምሻውን ይዞት በወጣው መረጃ የባለንድኦር አሸናፊው ቤንዜማ ሪያል ማድሪድን በመልቀቅ ከአል ኢቲሃደ ጋር የ3 ዓመት ውል ፈጽሟል፡፡…
የአፍሪካ ዞን 4 የጎልፍ ስፖርት ሻምፒዮና ውድድር የመክፈቻ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ዞን አራት የጎልፍ ስፖርት ሻምፒዮና ውድድር የመክፈቻ መርሐ ግብር ጦር ኃይሎች በሚገኘው ጎልፍ ክለብ እየተካሄደ ነው፡፡
በመክፈቻ መርሀ ግብሩ የባህልና ስፖርት ሚኒስትሩ ቀጄላ መርዳሳን ጨምሮ የስፖርት ዘርፍ…
የኢትዮጵያ ጠረጴዛ ቴኒስ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 2ኛው ዙር የኢትዮጵያ ጠረጴዛ ቴኒስ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ መካሄድ ጀምሯል።
የኢትዮጵያ ጠረጴዛ ቴኒስ ፌዴሬሽን ባዘጋጀው ውድድር ከስድስት ክለቦች የተውጣጡ ከ90 በላይ ስፖርተኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
ውድድሩ…
ዝላታን ኢብራሂሞቪች ከእግርኳስ ራሱን አገለለ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ስዊድናዊው አጥቂ ዝላታን ኢብራሂሞቪች በ41 ዓመቱ ራሱን ከእግርኳስ ዓለም ራሱን አግሏል፡፡
ግዙፉ አጥቂ በማልሞ፣ አያክስ፣ ጁቬንቱስ፣ ኢንተርሚላን፣ ኤሲሚላን፣ ባርሴሎና፣ ማንቼስተር ዩናይትድ፣ ፓሪ ሴንት ዥርሜን እና ኤል ኤ ጋላክሲ ክለቦች…
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በስዊድን ስቶክሆልም ማራቶን በሁለቱም ጾታዎች አሸንፈዋል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በስዊድን ስቶክሆልም ማራቶን ውድድር በሁለቱም ጾታዎች ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ በመያዝ በበላይነት አጠናቀዋል።
በሳምንቱ መጨረሻ በተለያዩ ሀገራት የአትሌቲክስ ውድድሮች ተካሂደዋል።
በሳምንቱ ከተደረጉ ውድድሮች…
በፕሪሚየር ሊጉ ባህርዳር ከነማ መቻልን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ27ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባህርዳር ከነማ መቻልን 3 ለ 2 በማሸነፍ የዋንጫ ተፎካካሪነቱን አጠናክሯል፡፡
ቀን 10 ሰዓት ላይ በተከናወነው መርሃ ግብር ሀብታሙ ታደሰ ሁለት ጎሎችን ለባህርዳር ከነማ ሲያስቆጥር የምንትስኖት…