Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

ዓለምአቀፋዊ ዜና

ከርዕደ-መሬት አደጋው 9 ቀናት በኋላ በሕይወት የተረፉ የ77 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ተገኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከቱርክ እና ሶሪያ ከደረሰው የርዕደ-መሬት አደጋ ዘጠኝ ቀናት በኋላ አንዲት የ77 ዓመት ዕድሜ ባለፀጋ ሴት በሕይወት መገኘታቸው ተገለጸ፡፡ ግለሰቧ አዲያማን በተባለች በደቡብ ምሥራቅ ቱርክ በምትገኝ አካባቢ ፍርስራሽ ውስጥ ነው በሕይወት ተገኙት፡፡…

በኬንያ ያጋጠመውን ድርቅ ተከትሎ ብሔራዊ የፀሎት ቀን ታወጀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)በኬንያ ለ 6 ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች ባለመዝነቡ ያጋጠመውን ከፍተኛ ድርቅ ተከትሎ በዛሬው ዕለት ብሔራዊ የፀሎት ቀን ታወጀ፡፡ አዋጁን ያስነገሩት የሀገሪቷ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ናቸው ተብሏል፡፡ ፕሬዚዳንት ሩቶ ለመጀመሪያ ጊዜ ዕለተ-ዕሁድ…

ሩሲያ “ለወዳጅ” ሀገራት ነዳጅ የምትልክበትን አቅጣጫ ልትቀይር መሆኑን ገለጸች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ “ለወዳጅ” ሀገራት ነዳጅ የምትልክበትን አቅጣጫ ልትቀይር መሆኑን የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ኖቫክ ተናገሩ፡፡ ሩሲያ በዚህ አመት የዘይት እና የነዳጅ ምርቶቿን ወደ “ወዳጅ” ሀገራት ለመላክ እና አጠቃላይ አቅርቦቱንም ከ75…

አሜሪካ ኖርድ ስትሪም የጋዝ ማስተላለፊያ መስመርን ሳታፈነዳ አልቀረም ተባለ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 6 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ ከሞስኮ ወደ በርሊን የተዘረጋውን “ኖርድ ስትሪም” የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር ሳታፈነዳ አልቀረም ተባለ፡፡ የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ እንደሚሉት አሜሪካ የሩሲያን እና የጀርመንን ትብብር እንደ ሥጋት ትመለከተዋለች፡፡…

የአሜሪካ ጦር በካናዳ አየር ክልል ምንነቱ ያልታወቀ በራሪ ቁስ መትቶ መጣሉን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካ ጦር ለጊዜው ምንነቱ ያልታወቀ በራሪ ቁስ በሰሜን ምዕራብ ካናዳ አየር ክልል ውስጥ መትቶ መጣሉ ተሰምቷል፡፡ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስቴር ጀስቲን ትሩዶ ÷ ምንነቱ ያልታወቀው ቁስ አካል በአሜሪካ ኤፍ-22 በተሰኘ ተዋጊ ጄት ተመትቶ መውደቁን…

በቱርክ እና ሶሪያ በመሬት መንቀጥቀጥ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከ21 ሺህ ባለይ መድረሱ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቱርክ እና ሶሪያ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር 21 ሺህ መድረሱ ተገለፀ፡፡ የነፍስ አድን ሰራተኞች አሁንም በሕይወት የተረፉ ሰዎችን ለማግኘት ፍለጋ እያደረጉ ሲሆን ነገር ግን አደጋው ከተከሰተ አራተኛ ቀን…

በቱርክና ሶሪያ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 17 ሺህን አለፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰኞ በደቡባዊ ቱርክ እና ሰሜናዊ ሶሪያ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 17 ሺህ ማለፉ ተገለጸ፡፡ ከአደጋው የተረፉ ሰዎች ሊኖሩ ቢችሉም፥ መጠለያዎች በመውደማቸው ፣ “የውሃ፣ ነዳጅ እና የኤሌክትሪክ አገልግሎት በመቋረጡ ተጨማሪ…

ሩሲያ በ77 አሜሪካውያን ላይ ማዕቀብ ጣለች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ 33 ከፍተኛ የዴሞክራትና የሪፐብሊካን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ቤተሰቦችን ጨምሮ በ77 አሜሪካውያን ላይ ማዕቀብ ጥላለች። ሞስኮ ማዕቀቡን የጣለችው ዋሺንግተን "የሩሲያን ጦር ይረዳሉ" ባለቻቸው 22 ግለሰቦች ላይ ማዕቀብ ከጣለች ከአንድ…

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኬንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ጀመሩ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 1 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኬንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ጀመሩ፡፡ ፕሬዚዳንቱ ናይሮቢ ጆሞ ኬንያታ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የኬንያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አልፍሬድ ሙታ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ለሁለት ቀናት በሚያደርጉት…

በቱርክ እና ሶሪያ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከ11 ሺህ ማለፉ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቱርክ እና በሶሪያ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሟቾች ቁጥር ከ11 ሺህ በላይ መድረሱ ተገልጿል። የቱርኩ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይፕ ኤርዶኻን ዛሬ እንደገለፁት÷ በቱርክ ቢያንስ 8 ሺህ 574 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል። በሶሪያ ደግሞ…