Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

ዓለምአቀፋዊ ዜና

የዓለም ሥርዓት ወደ ብዝኃ-መር መቀየር አለበት – ቻይና

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የዓለም ሥርዓት ከአንድ ብቻ መር ወደ ብዝኃ-መር መቀየር እንዳለበት ቻይና አስገነዘበች፡፡ የሀገሪቱ ከፍተኛ ምክር ቤት ዓመታዊ ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል። በዚሁ ወቅት የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ እንዳሉት፤ ሀገራቸው የተሻለ ዓለም…

በጃፓን በተቀሰቀሰው የሰደድ እሳት ከ4 ሺህ በላይ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቀሉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጃፓን የተከሰተው ሰደድ እሳት በግማሽ ክፍል ዘመን ታይቶ የማይታወቅና ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ሰደድ እሳቱን ለማጥፋት 2 ሺህ የሚሆኑ የአየር እና የምድር የእሳት አደጋ ሰራተኞች ጥረት እያደረጉ ቢሆንም÷ ለመቆጣጠር አዳጋች…

አሜሪካ ለዩክሬን የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ ለጊዜው ማቋረጧን አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ለዩክሬን የምታደርገው ወታደራዊ ድጋፍ በጊዜያዊነት እንዲቋረጥ መወሰናቸው ተገልጿል። ውሳኔው ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከዩክሬን አቻቸው ቮሎድሚር ዘለንስኪ ጋር ከቀናት በፊት በነጩ ቤተመንግስት…

ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ለአሜሪካ ክብር አልሰጡም -ፕሬዚዳንት ትራምፕ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ በነጩ ቤተመንግስት ያደረጉት ውይይት ያለስምምነት ተጠናቅቋል፡፡ ሁለቱ መሪዎች የሩሲያ እና ዩክሬንን ጦርነት በሰላማዊ ውይይት መቋጨት በሚቻልበት ሁኔታ ለመምከርና…

ኢጋድ የሴቶች ዐቅም የማጎልበት ሥራን እንደሚያጠናክር አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) የሴቶችን ዐቅም የማጎልበት ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የተቋሙ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ዋና ፀሐፊው በተቋሙ በተዘጋጀ የሴቶች ዐቅም ግንባታ ሥልጠና ላይ ተገኝተው…

ሩሲያ ከፍተኛ ዲፕሎማቶቿን ወደ ሳዑዲ ላከች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሩሲያ ከአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር የሚወያይ ከፍተኛ የዲፕሎማቶች ልዑኳን ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ መላኳን አስታወቃለች፡፡ ልዑኩ በሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ እና የክሬሚሊን ከፍተኛ አማካሪ በሆኑት ዩሪ ኡሽኮቭ የተመራ መሆኑ…

የአሜሪካ ባለስልጣናት ከሩሲያ ጋር ለሚደረገው ንግግር ወደ ሳዑዲ ሊያቀኑ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካ የመካከለኛው ምስራቅ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ የዩክሬኑን ጦርነት ለማስቆም ከሩሲያ ጋር በሳዑዲ አረቢያ በሚደረገው ንግግር ላይ ለመሳተፍ ከብሔራዊ ደህንነት አማካሪው ማይክ ዋልትዝ ጋር እንደሚጓዙ አስታወቁ። የአሜሪካ እና ሩሲያ…

አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እስክታገኝ ድረስ ጥረት ማድረግ እንደሚቀጥሉ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እስክታገኝ ድረስ ጥረት ማድረግ እንደሚቀጥሉ የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸኃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ። እየተካሄደ በሚገኘው 38 የአፍሪካ ህብረት መሪዎች ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ዋና ጸኃፊው አንቶኒዮ…

ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከሩሲያና ቻይና አቻዎቻቸው ጋር በወታደራዊ በጀት ቅነሳ ዙሪያ መወያየት እንደሚፈልጉ ተናገሩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና ከቻይና ፕሬዚዳንት ዢ ሺንፒንግ ጋር የሦስቱንም ሀገራት የኒውክሌር ክምችት ለመቀነስ እና የወታደራዊ በጀታቸውን በግማሽ በመቀነስ ላይ ለመወያየት ሀሳብ አቅርበዋል። ትራምፕ…

ትራምፕ እና ፑቲን የዩክሬን እና ሩሲያን ጦርነት ለማስቆም ድርድር እንዲጀመር ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሩሲያ ዩክሬን ያለውን ጦርነት ማስቆም የሚያስችል ድርድር በፍጥነት እንዲጀመር ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር መነጋገራቸውን ገለጹ። ትራምፕ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ÷"ቡድኖች…