Browsing Category
ዓለምአቀፋዊ ዜና
ኢራን ከሞሳድ ጋር ግንኙነት አላቸው ያለቻቸውን ከ700 በላይ ዜጎች አሰረች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢራን ከእስራኤል የስለላ ድርጅት ሞሳድ ጋር ግንኙነት አላቸው ያለቻቸውን ከ700 በላይ ዜጎች ማሰሯ ተነገረ፡፡
ባለፉት 12 ቀናት ብቻ ኢራን ከ700 በላይ ዜጎችን ከእስራኤል ጋር ግንኙነት በመፍጠር እያሴሩ ነው በሚል ጥርጣሬ ማሰሯን ፋርስ የዜና…
“እስራኤልና ኢራን የተኩስ አቁም ለማድረግ ተስማምተዋል” ፕሬዚዳንት ትራምፕ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) እስራኤል እና ኢራን ዘላቂ የተኩስ አቁም ለማድረግ ተስማምተዋል አሉ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ እንዳሉት÷ እስራኤልና ኢራን ላለፉት 12 ቀናት ሲያካሄዱት የቆዩትን ጦርነት ለማቆም ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የኢራን…
ኢራን ኳታር በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ ጥቃት ፈጸመች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢራን ኳታር በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ የሚሳኤል ጥቃት ፈጽማለች፡፡
ጥቃቱን ተከትሎ በዶሃ ከፍተኛ ፍንዳታ የተሰማ ሲሆን÷ በኳታር የሚገኘው እና አሉዴይድ የተሰኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር በጥቃቱ ኢላማ ተደርጓል፡፡
በሀገሪቱ የአሜሪካ…
በኢራን ግዙፍ የኒውክሌር ማዕከል ላይ በድጋሚ ጥቃት ተፈጸመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢራን ግዙፍ የኒውክሌር ማዕከል የሆነው ፎርዶው በዛሬው ዕለት በድጋሚ ጥቃት እንደተፈጸመበት የአካባቢው ባለስልጣናት ተናገሩ፡፡
አሜሪካ በትናንትናው ዕለት ፎርዶውን ጨምሮ ናታንዝ እና ኢስፋሃን በተሰኙ የኢራን የኒውክሌር ጣቢያዎች ላይ የተሳካ…
በኢራን የኒውክሌር ማዕከላት ላይ ከፍተኛ ውድመት ደርሷል – አሜሪካ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሶስት የኢራን ኒውክሌር ማዕከላት ላይ ከፍተኛ ውድመት አድርሻለሁ አለ የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር፡፡
የአሜሪካ ጦር አውሮፕላኖች ኢራን ውስጥ በሚገኙ ሦስት የኒውክሌር ማዕከላት ላይ በዛሬው ዕለት ንጋት ላይ ጥቃት መፈጸማቸው ይታወሳል፡፡…
ኢራን በአሜሪካ ለተፈጸመባት ጥቃት አጸፋዊ ርምጃ እወስዳለሁ አለች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢራን በሦስት የኒውክሌር ማዕከላት ላይ አሜሪካ ለፈጸመችባት ጥቃት የአጸፋ ርምጃ ለመውሰድ ሁሉም አማራጮች በጠረጴዛ ላይ ናቸው ስትል አስጠንቅቃለች።
አሜሪካ ከሰዓታት በፊት ግዙፉን ፎርዶው የኒውክሌር ተቋም ጨምሮ በሦስት የኢራን…
የእስራኤል እና ኢራን ግጭት መፍትሄ አለው – ፕሬዚዳንት ፑቲን
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የእስራኤል እና ኢራን ግጭት በእርግጠኝነት መፍትሄ ይገኝለታል አሉ፡፡
አንድ ሳምንት ያስቆጠረውን የእስራኤል እና ኢራን ግጭት ለማስቆም ሩሲያ ከሀገራቱ ጋር ንግግር እያደረገች መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ…
ኢራን እና እስራኤል ጥቃት መሰናዘራቸውን ቀጥለዋል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) እየተባባሰ በመጣው የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ኢራን በደቡባዊ እስራኤል በምትገኘው የቢርሼባ ከተማ የሚሳኤል ጥቃት ፈፅማለች፡፡
በጥቃቱ በከተማዋ የሚገኘው ሶሮካ ሆስፒታል ኢላማ መደረጉ በእስራኤል በኩል የተገለጸ ሲሆን፤ 30 ሰዎች ጉዳት…
አሜሪካ ጣልቃ የምትገባ ከሆነ ከፍተኛ አደጋ ሊከሰት ይችላል- አያቶላህ አሊ ሀሚኒ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢራን እና እስራኤል ግጭት አሜሪካ ወታደራዊ ተሳትፎ ካደረገች ከፍተኛ አደጋ ሊከሰት ይችላል ሲሉ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ሀሚኒ አስጠነቀቁ፡፡
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በፍጥነት እጅ እንድትስጥ ማሳሰባቸውን ተከትሎ…
የኢራን መሪ የት እንዳሉ ብናውቅም አሁን ላይ እንዲገደሉ አንፈልግም – ፕሬዚዳንት ትራምፕ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ሀሚኒ የት እንደተደበቁ እንደሚያውቁና ቢያንስ አሁን ላይ እሳቸውን ለመግደል እንደማይፈልጉ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ተናገሩ፡፡
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራኑ መሪ በትክክል የት እንዳሉ…