Fana: At a Speed of Life!

የተከሰቱ ግጭቶች ዜጎች በህይወት እና ንብረታቸው ላይ መተማመን እንዲያጡ አድርጓል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የተከሰቱ ግጭቶች እና አለመረጋጋት ዜጎች በህይወት እና ንብረታቸው ላይ መተማመን እንዲያጡ ማድረጉን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ የተከሰተው አለመረጋጋት በሰው ህይወት፣ በአምራች ተቋማት፣ በግል እና መንግስት ሃብቶች ላይ…

በአቶ ደመቀ መኮንን የተመራ ልዑክ ሳዑዲ ዓረቢያ ሪያድ ገባ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተመራ ልዑክ ሳዑዲ ዓረቢያ ሪያድ ገብቷል፡፡ ልዑካኑ ኪንግ ካሊድ አውሮፕላን ማረፊያ ሲድርስ የሳዑዲ ዓረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ በሳዑዲ ዓረቢያ የኢፌዴሪ አምባሳደር ሌንጮ ባቲ እና…

በአዲስ አበባ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር 17 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር 17 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ማድረጉን የከተማዋ ውበት እና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ገለጸ። የቢሮው ምክትል ኃላፊ ይመኙሻል ታደሰ እንዳሉት÷ በሁለተኛው ምዕራፍ 17 ሚሊየን…

በግሪክ የኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት ላይ ምርመራ መጀመሩን የፍትሕ ሚኒስቴር አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በግሪክ የኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት ላይ በወንጀል ጥርጣሬ በደረሰ ጥቆማ ምርመራ መጀመሩን የፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ፍትሕ ሚኒስቴር የትምህርት ቤቱ የቀድሞ ቦርድና አስተዳደር ከተለያዩ ወንጀሎች ጋር ተያይዞ በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ…

አልሸባብ ሊፈፅም የሞከረው የጥፋት ሴራ በመከላከያ ሠራዊቱ ጥንካሬ ሙሉ በሙሉ መክሸፉን የመከላከያ ሰራዊት ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አልሸባብ ሊፈፅም የሞከረው የጥፋት ሴራ በመከላከያ ሠራዊቱ ጥንካሬ ሙሉ በሙሉ መክሸፉን የመከላከያ ሰራዊት ገለጸ። አልሸባብ በተለያየ ጊዜ በምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል ስጋት ለመፍጠር የጥፋት ሙከራዎችን ቢያደርግም በጀግኖች ኢትዮጵያውያን…

ከአውስትራሊያ ጋር በክህሎት ልማት እና በሥራ ዕድል ፈጠራ በጋራ መስራት በሚቻልበት አግባብ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአውስትራሊያ ጋር በክህሎት ልማት እና በሥራ ዕድል ፈጠራ በጋራ መስራት በሚቻልበት አግባብ ላይ ተወያየ። በዚህ ወቅት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሡ ጥላሁን በኢትዮጵያ በኩል የሰለጠነ እና…

ግብረ ኃይሉ በመዲናዋ የፀጥታ ችግሮችን ለመፍጠር የተዘጋጁ ኃይሎች እንዳሉ ደርሼባቸዋለሁ አለ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ የፀጥታ ችግሮችን ለመፍጠር የተዘጋጁ ኃይሎች እንዳሉ ደርሼባቸዋለሁ ሲል ገልጿል፡፡ የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል መግለጫ ሰጥቷል፡፡ በመግለጫውም ፥ የፀጥታ እና…

ጀርመን በተለያዩ ጉዳዮች ከኢትዮጵያ ጋር የምታደርገውን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ አለምአንተ አግደው የጀርመን የኢኮኖሚ ትብብርና ልማት ሚኒስትር ዮአኪን ፍላስባርዝ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው ተወያይተዋል፡፡ ሚኒስትር ዴዔታ አለምአንተ አግደው እና ሚኒስትር ዮአኪን ፍላስባርዝ ጨምሮ በኢትዮጵያ የጀርመን…

ሪያል ማድሪድ እና ቦሩሲያ ዶርትሙንድ  በቤሊንግሃም ዝውውር ሲስማሙ ሊዮኔል ሜሲ ወደ አሜሪካ ሊያቀና ነው

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሪያል ማድሪድ እንግሊዛዊውን የቦሩሲያ ዶርትመንድ አማካይ ጁዲ ቤሊንግሃምን ለማስፈረም መስማማቱ ተሰምቷል። ሎስብላንኮዎች አማካዩን ለማስፈረም 113 ሚሊየን ፓውንድ የሚከፍሉ ሲሆን፥ ተጫዋቹም ስድስት አመታት የኮንትራት ውል እንደሚፈርም…