Fana: At a Speed of Life!

የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ዛሬ ሌሊት 9 ጊዜ መድፍ ይተኮሳል

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 7 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ነገ የሚከበረውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ 9 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ በመከላከያ ሚኒስቴር የስነ ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት ማስታወቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። በኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር የስነ ልቦና ግንባታ ዋና…

የሀይማኖት አባቶች ለትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 7 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የተገኘውን ሰላም፣ ክርስቲያኑ ምዕመን በጎ ተግባራትን በማከናወን ሊተገብር እንደሚገባ የሀይማኖት አባቶች አሳሰቡ። የሀይማኖት አባቶቹ የትንሣኤ በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።…

የኦሮሚያ እና የሶማሌ ክልል ከፍተኛ አመራሮች የጋራ ስብሰባ በድሬዳዋ ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 7 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ እና የሶማሌ ክልል ከፍተኛ አመራሮች የጋራ ስብሰባ የሁሉቱም ክልል ርዕሳነ- መስተዳድሮች በተገኙበት በድሬዳዋ ከተማ ተካሂዷል፡፡ ሁለቱ ክልሎች በሰባት ዞኖች የሚዋሰኑ እና ለረዥም ዘመናት የጋራ ባህል እና ታሪክ ተጋርተው የኖሩ ህዝቦች…

የኢትዮጵያውያን እና የዳያስፖራ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፎረም በዋሺንግተን ዲሲ ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 7 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የተሰማሩ ባለሃብቶች እና ነዋሪነታቸውን በአሜሪካ ያደረጉ ኢትዮጵያውያን የዳያስፖራ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፎረም በዋሺንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተካሄደ። የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ…

የዓለም ባንክ በበጀት ድጋፍና በብድር መልክ ጠንካራ ድጋፍ ለኢትዮጵያ እንደሚያደርግ አረጋገጠ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት ዴቪድ ማልፓስ ጋር ተወያዩ። በዚህም ወቅት በኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። ፕሬዚዳንቱ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመተግበሩ የኢትዮጵያ መንግስት ያሳካውን…

ለክትባት ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታ 30 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ የክትባት ማምረቻ ፋብሪካ ለመገንባት የሚያስችል 30 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ ማድረጉ ተገለጸ፡፡ በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለዚሁ ዓላማ የሚገነባው የክትባት ፋብሪካ ባለሀብቶችን የሚያሳትፍ መሆኑ ተገልጿል።…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለጣልያን ጠቅላይ ሚንስትር የእራት ግብዣ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለጣልያን ጠቅላይ ሚንስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በታላቁ ቤተ መንግስት የክብር የእራት ግብዣ አደረጉ። በታላቁ ቤተ መንግስት በተደረገው የክብር እራት ግብዣ ጠቅላይ ሚኒስትሮቹ የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን ከጠቅላይ…

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝነት በጋራ ስምምነት መለያየታቸው ተገለጸ፡፡ ተሰናባቹ አሰልጣኝ ከመስከረም 2013 ዓ.ም ጀምረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን በዋና አሰልጣኝነት መርተዋል፡፡ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ…

አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና ሙስጠፌ መሀመድ በድሬዳዋ በተካሄደው የኢፍጣር ሥነ ስርዓት ተሳተፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልልርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ በድሬዳዋ ከተማ በተካሄደው የኢፍጣር ሥነ ስርዓት ላይ ተሳተፉ፡፡ በኢፍጣር ሥነ ስርዓቱ ላይ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃርን ጨምሮ…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሶማሊያውን ፕሬዚዳንት ተቀበሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሶማሊያውን ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸውን ገለጹ። ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም…