Fana: At a Speed of Life!

ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ በኢትዮጵያ ከጣሊያን አምባሳደር ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ በኢትዮጵያ ከጣሊያን አምባሳደር  አጎስቲኖ ፓልሴ ጋር የተፈናቀሉ ወገኖችን መረዳት በሚቻልበት ሁኔታ እና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። በውይይቱ የጣሊያን ኤምባሲ ካውንስለር አሪያና ካታላኖ፣…

የጤና ሚኒስቴር ለትግራይ ክልል የሚያስፈልጉ መድሃኒት እና የህክምና ቁሳቁሶች መቅረብ መቀጠላቸውን አስታወቀ 

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ የጤና ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶ ጋር በመሆን ለትግራይ ክልል የተቀናጀ የጤና እና የስነ ምግብ አገልግሎት ማቅረብ መቀጠሉን አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ከኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ከብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር በመሆን…

ለትግራይ ክልል ከባለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ 2 ነጥብ 1 ቢሊየን ብርና 87 ሺህ ሜትሪክ ቶን ምግብ ተልኳል- የጠቅላይሚኒስትር ጽህፈት ቤት

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለትግራይ ክልል ከባለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ 2 ነጥብ 1 ቢሊየን ጥሬ ብር፣ 87 ሺህ ሜትሪክ ቶን ምግብ እና ከ783 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ መላኩን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ…

የኢትዮጵያና ብሪታንያ ባለሀብቶች በጋራ ለመስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያና ብሪታንያ ባለሀብቶች በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሔደ፡፡ የእንግሊዝ ኤምባሲ ያዘጋጀው ይሄው ውይይት፥ የንግዱን ማህበረሰብ ማቀራረብና አብረው መስራት የሚችሉባቸው ሁኔታዎችን መፍጠር ያለመ እንደሆነ…

በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ነዋሪዎች የሕግ ማስከበር ተግባሩን በመደገፍ ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ነዋሪዎች መንግስት እየወሰደ ያለውን ሕግ የማስከበር ተግባር እንደሚደግፉ በሰላማዊ ሰልፍ ገለጹ። የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና አባገዳዎች ጭምር የተሳተፉበት ሰላማዊ ሰልፉ በዞኑ ሦስት…

ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ የ210 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ አገኘች

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ ቆላማ በሆኑ አካባቢዎች የከርሰ ምድር ውሃን ለማልማትና ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል የ210 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ አገኘች፡፡ ድጋፉ የዝናብ እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች የከርሰ ምድር ውሃን በማልማት ለመጠጥ…

ከ110 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባሳለፍነው ሳምንት 110 ሚሊየን 66 ሺህ ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የገቢና የወጪ የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡   ኮሚሽኑ ባሳለፍነው ሳምንት በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ባደረገው…

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በልደታ ክ/ ከተማ አዲስ የንግድ እና የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ አስጀመሩ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በልደታ ክፍለ ከተማ አዲስ የንግድ እና የመኖሪያ ቤቶች ግንባታን በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምረዋል፡፡   ከንቲባዋ አጠቃላይ 36 ቤቶች ግንባታ ያስጀመሩ ሲሆን÷ ከእነዚህም…

በጋምቤላ በክረምቱ የወባ ወረርሽኝ እንዳይከሰት የመከላከል ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ተባለ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 29 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው ክረምት የወባ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የኮሙኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ በላይነህ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የወባ…

በግለሰብ ቤት የሞርታር ተተኳሽ ተደብቆ ተገኘ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 29 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ ልዩ ስሙ 02 ቀበሌ ጢሳ አባሊማ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በግለሰብ መፀዳጃ ቤት ውስጥ 23 የሞርታር ተተኳሽ መገኘቱን የአምባሰል ወረዳ ሚሊሻ ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ተተኳሾ ከኀብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት…