Fana: At a Speed of Life!

በእንጅባራ ከአንዲት እናት 24 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕጢ በቀዶ ሕክምና ተወገደ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል ከአንዲት እናት 24 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕጢ በቀዶ ሕክምና መወገዱ ተገልጿል፡፡ የ38 ዓመት ታካሚዋ ወ/ሮ ትሁን ገነቱ በፓዌ ልዩ ወረዳ ነዋሪ ሲሆኑ÷ሁለት ሰዓት አካባቢ የወሰደ የተሳካ ከባድ ቀዶ ሕክምና አድርገው…

የአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ እንዲያገኙ የታየው ቁርጠኝነት ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት መሪዎች የአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ እንዲያገኙ ያሳዩት ቁርጠኝነትና አጋርነት ለሌሎች ምሳሌ እንደሚሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ እና የደቡባዊ አፍሪካ የልማት…

አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው የግማሽ ማራቶን አሸናፊ ሆነች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በዱባይ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው አሸናፊ ሆናለች። አትሌት ያለምዘርፍ 1 ስዓት ከ7ደቂቃ ከ09 ሴኮንድ በመግባት ውድድሩን በአንደኝነት ማጠናቀቋን የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ አመላክቷል።

13ኛው የሀዋሳ ሐይቅ ግማሽ ማራቶን ውድድር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 13ኛው የሀዋሳ ሐይቅ ግማሽ ማራቶን ውድድር ተካሄደ፡፡ 21ኪሎ ሜትር በሸፈነው በዚህ ውድድር በወንዶች አትሌት አስቻለው ብሩ ፣በሴቶች ደግሞ ምህረት ገመዳ አሸንፈዋል።…

ጨፌ ኦሮሚያ 8ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጨፌ ኦሮሚያ የ4ኛ ዓመት 8ኛ መደበኛ ጉባዔውን በአዳማ ከተማ ገልመ አባገዳ ማካሄድ ጀምሯል። በአባገዳዎች ምርቃት የጀመረው መደበኛ ጉባኤው በተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። በጉባኤው…

“በአሁኑ ወቅት የኮሪደር ልማት በአማራ ክልል ሰባት ከተሞች በመስፋፋት ላይ ይግኛል፡፡”- የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት

የኮሪደር ልማት በከተሞቹ የራስ ዐቅም፣ ከሕዝብ ተሳትፎ፣ ከፌደራልና ከልዩ ልዩ ድጋፎች በሚገኝ ዐቅም እየተተገበረ ነው። በባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ እና ወልድያ ከተሞች ተጀምሮ 32.23 ኪ.ሜ መንገድ 27.04 ሄር አረንጓዴና ፓርክ ልማት፣ 3.7 ሄ/ር…

በቦረና ሳይንት ብሔራዊ ፓርክ እና በጉና ተራራ  ጥብቅ ስፍራ የተከሰተው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ዋለ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሔራዊ ፓርክ እና በደቡብ ጎንደር ዞን የጉና ተራራ የማህበረሰብ ጥብቅ ስፍራ የተከሰተው የእሳት አደጋ በህብረተሰቡ እና አጋር አካላት ትብብር በቁጥጥር ስር ውሏል። የወረሂመኖ ብሔራዊ ፓርክ…

አይኤምኤፍ ለኢኮኖሚ ሪፎርም ፕሮግራማችን የሚያደርገውን የቀጠለ ድጋፍ ዋጋ እንሰጠዋለን – ጠ/ሚ ዐቢይ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አይኤምኤፍ ለኢኮኖሚ ሪፎርም ፕሮግራማችን የሚያደርገውን የቀጠለ ድጋፍ ዋጋ እንሰጠዋለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ፥ የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም…

በ800 ሜትር የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አትሌት ፅጌ ድጉማ ድል ቀናት

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንሳይ ሜዝ በተካሄደ የ800 ሜትር የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ውድድር እትሌት ፅጌ ድጉማ አሸንፋለች፡፡ ፅጌ የ800 ሜትሩን 1 ደቂቃ ከ58 ሴኮንድ ከ97 ማይክሮ ሴኮንድ በመጨረስ በቀዳሚነት ማጠናቀቋን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ…

በመዲናዋ የኮሪደር ልማት ስራን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ይሰራል – ከንቲባ አዳነች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ስራን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ፡፡ ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስርገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፥ የሥድስት ወራት የስራ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡…