Fana: At a Speed of Life!

በአማራና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ተከስቶ በነበረው ግጭት ተፈናቅለው የነበሩ 4 ሺህ 541 ሰዎች ወደ ነበሩበት ዳንጉር ወረዳ ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፈው ዓመት በመተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ በተቀሰቀሰው ግጭት ከቀያቸው ተፈናቅለው በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ተጠልለው የነበሩ 4 ሺህ 541 ሰዎች በዛሬው ዕለት ወደ ነበሩበት መመለሳቸውን የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግርማ ታደሰ…

ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የአውሮፓ እና የአሜሪካ ሃገራት አምባሳደሮች በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ገለፃ ተደረገ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 17 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከውሃ፣ መስኖና ኢነርጅ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የአውሮፓ እና አሜሪካ ሃገራት አምባሳደሮች ስለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ገለጻ አድርጓል።   ገለጻው በኢፌዴሪ…

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ደንብ እና የመመሪያዎች አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማሻሻል ለፖሊስ አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል በታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ደንብ እና መመሪያዎች አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማሻሻል ለፖሊስ አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታወቀ። ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ…

ኢትዮጵያ አሁን ያላት አቅም የቫይረሱን ስርጭት መከላከልና መቆጣጠር ብቻ እንደሆነ ተገንዝቦ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ አሁን ያላት አቅም የቫይረሱን ስርጭት መከላከልና መቆጣጠር ብቻ እንደሆነ ተገንዝቦ መስራት እንደሚገባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መሪማሪ ቦርድ አሳሰበ። መሪማሪ ቦርዱ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን መከላከልና መቆጣጠር አስመልክቶ በሰንዳፋ…

በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ ታማሚ እናት ከኮቪድ19 ነጻ የሆነ ህጻን ተገላገለች

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 17 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሮና ቫይረስ በላቦራቶሪ ምርምራ ተገኝቶባት በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የለይቶ ህክምና ማዕከል ውስጥ ክትትል እየተደረገላት የምትገኘው የ34 ዓመት እናት 3 ነጥብ 1 ኪሎ ግራም የሚመዝን ወንድ ልጅ በቀዶ ህክምና በሰላም ተገላግላለች። ከህጻኑ…

አውስትራሊያ ከወራት በፊት ተቀስቅሶ በነበረው ሰደድ እሳት ጉዳይ ላይ ምርመራ ጀመረች

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 17 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) አውስትራሊያ ባለፈው መስከረም ወር ተቀስቅሶ በነበረው ሰደድ እሳት ጉዳይ ላይ ምርመራ ጀመረች። የሰደድ እሳት ጉዳዮችን የሚመለከተው ኮሚሽንም ረጅም ጊዜ የሚወስደውን ምርመራ በዛሬው እለተ መጀመሩን አስታውቋል። በምርመራው የደረሰው አጠቃላይ…

የአፍሪካ ቀን ዛሬ በመላው አህጉሪቱ ታስቦ ዋለ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በየዓመቱ በአውሮፓውያኑ የቀን አቆጣጠር ግንቦት 25 የሚከበረው የአፍሪካ ቀን ዛሬም በመላው አህጉሪቱ ታስቦ ውሏል። ከዚህ ቀደብ በአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር የቆየው እለቱ ዛሬ በቪዲዮ በሚካሄድ ኮንፈረንስ ታስቦ መዋሉን…

በሰራባ ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ 230 ህገ ወጥ የቱርክ ሽጉጥ ተያዘ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በሰራባ ጉምሩክ መቆጣጠሪያ ጣቢያ በተደረገ ፍተሻ 230 ህገወጥ የቱርክ ሽጉጥ መያዙ ተገለፀ። ህገ ወጥ የጦር መሳሪያው ከሼህዲ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ ኒሳን ፓትሮል ሲንግል ሚኒካፕ በሆነ የግል መኪና ላይ በትናትናው ዕለት በሰራባ ጉምሩክ…