Fana: At a Speed of Life!

ከተማ አስተዳደሩ ከፌደራል ፖሊስ ጎን ሆኖ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ያደርጋል-ከንቲባ አዳነች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚችለው ሁሉ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጎን ሆኖ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ያደርጋል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና በአስተዳደሩ ከከፍተኛ እስከ…

የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎችን ማስፋፋት ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ጤናማ ትውልድ ለመገንባት የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎችን ማስፋፋት ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ አቶ ተመስገን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ዲፖ…

ከተባበርን ጠንካራ ቀጣና መፍጠር እንችላለን – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ከተባበርን እና ከተደጋገፍን ሁላችንም በጋራ በመልማት ጠንካራ ቀጣና መፍጠር እንችላለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ፡፡ የናይል ወንዝ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት ከዛሬ ጀምሮ ወደ ተፈጻሚነት ገብቷል፡፡ ይህን ተከትሎ…

ባለሀብቶች በቅንጅት በመሥራት የክልሉን ብልጽግና ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በክልሉ የሚገኙ ባለሀብቶች ተደምረውና ተቀናጅተው በመሥራት የክልሉን ብልጽግና ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ፡፡ ርዕሰ መሥተዳድሩ በዎላይታ ዞን ቦዶቲ ከተማ ከ100 ሚሊየን ብር በሚልቅ ወጪ…

መልካ አቴቴ፣ መልካ ዶሻ እና መልካ ሰበታ የኢሬቻ በዓላት እየተከበሩ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2017 ዓ.ም የመልካ አቴቴ፣ መልካ ዶሻ እና መልካ ሰበታ ኢሬቻ በዓላት በተለያዩ አካባቢዎች እየተከበሩ ነው፡፡ በበዓላቱ አከባበር ላይ አባ ገዳዎች፣ ሀደ ሲንቄዎች፣ ቄሮዎች እና ቀሬዎችን ጨምሮ የየአካባቢዎቹ ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡ በዓላቱ…

የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር አዋሽ አካባቢ መጠነኛ ጉዳት አጋጠመው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር አዋሽ አካባቢ መጠነኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለጸ፡፡ 15 ሜትር ርዝመት ያለው የባቡር ሃዲዱ ብረት ወደ መሬት መስጠሙን እና አንዳንድ የሃዲዱ ማሰሪያዎች መቆራረጣቸውም ተገልጿል፡፡ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አክሲዮን…

የክልሉ ምክር ቤት የ2017 የሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም መገምገም ጀምረ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተዳደር ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት የሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን መገምገም  ጀምሯል። ምክር ቤቱ በተያዘው የ2017 በጀት ዓመት ያለፉት ሦስት ወራት የዕቅዶችን አፈጻጸም በመገምገም ጥንካሬዎችን ፣ ውስንነቶችን…

በአዲስ አበባ ማዕከል ስልጠና እየወሰዱ ያሉ አመራሮች የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ዙር ሥልጠናን በአዲስ አበባ ማዕከል እየወሰዱ ያሉ አመራሮች በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ። በጉብኝታቸውም የመከላከያ ዋና መስሪያ ቤትን ጨምሮ በከተማዋ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት፣ የተቋማት የዲጂታል…

በአዋሽ ፈንታሌ ዛሬ ጠዋት ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ከጠዋቱ 1 ሠዓት ከ37 ገደማ በአዋሽ ፈንታሌ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 6 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ሠመራ ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት አደም አሊ ጉዳዩን አስመልክተው ለፋና…

የናይል ወንዝ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት ወደ ተፈጻሚነት ገባ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የናይል ወንዝ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት ከዛሬ ጀምሮ ወደ ተፈጻሚነት መግባቱን የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሐብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) አስታወቁ፡፡ ሚኒስትሩ ስምምነቱ ወደ ተፈጻሚነት መግባቱን አስመልክተው የናይል የትበብር ማዕቀፍ ስምምነት…