Fana: At a Speed of Life!

ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ቱቱ መላኩ የቢቢሲ የልዩነት ፈጣሪዎች ሽልማትን አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ቱቱ መላኩ የቢቢሲ የልዩነት ፈጣሪዎች ሽልማትን አሸንፋለች፡፡ ቱቱ መላኩ በምትኖርበት ከተማ ማህበረሰብ ውስጥ ልዩነት የሚፈጥር ሥራ አከናውናለች በሚል ነው ቢቢሲ ሬዲዮ ቤርክሻየር ሽልማቱን ያበረከተላት፡፡ ቢቢሲ ሬዲዮ…

ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ኢኮኖሚያዊ ትብብር ለማጠናከር እንደምትሰራ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ አዲስ ከተሾሙት በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር የንስ ሃንፌት ጋር ተወያይተዋል፡፡ አምባሳደር ምስጋኑ÷ ኢትዮጵያ እየተገበረችው ያለውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ብሔራዊ ምክክርና የሽግግር ፍትሕ…

አቶ አህመድ ሺዴ ከቻይና ዓለም አቀፍ ልማት ትብብር ኤጀንሲ ልዑክ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህምድ ሺዴ በቻይና ዓለም አቀፍ ልማት ትብብር ኤጀንሲ ምክትል ሊቀመንበር ዣኦ ፌንግታኦ ከተመራው ልዑክ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ አቶ አህመድ የኢትዮጵያ መንግስት የወሰዳቸውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብሮችንና…

ሃን ካንግ በስነ ጽሁፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት አሸናፊ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ደቡብ ኮሪያዊቷ ሃን ካንግ በስነ ጽሁፍ ዘርፍ የ2024 የኖቤል ሽልማት አሸናፊ መሆን ችለዋል፡፡ የ53 ዓመቷ ሃን የልብ ወለድ ደራሲ ከዚህ ቀደም በፈረንጆቹ 2007 በጻፉት ‘ዘ ቬጀተሪያን’ በተሰኘው መፅሐፋቸው አማካኝነት የ2016 ማን ቡከር…

ኢትዮጵያ በአፍሪካ የብስክሌት ሻምፒዮና 3ኛውን የነሐስ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኬንያ ኤልዶሬት እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ የብስክሌት ሻምፒዮና ድብልቅ ውድድር ኢትዮጵያ 3ኛውን የነሐስ ሜዳሊያ አግኝታለች። የአፍሪካ የብስክሌት ሻምፒዮና በኬንያ ኤልዶሬት ከትናንት ጀምሮ እየተካሄደ እንደሚገኝ የባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር…

የሀገር ውስጥ የቡና ተጠቃሚነት ትርጉም ባለው መልኩ እድገት አሳይቷል – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገር ውስጥ የቡና ተጠቃሚነት ትርጉም ባለው መልኩ እድገት አሳይቷል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ቡና የኢኮኖሚያችን ዋልታ ነው፤ በቡና…

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የሴኡል ስማርት ሲቲ 2024 ምርጥ አመራር ሽልማት አሸናፊ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በደቡብ ኮሪያ በተካሄደው የሴኡል ስማርት ሲቲ 2024 ምርጥ አመራር ሽልማት አሸናፊ በመሆን እውቅና ተበረከተላቸው፡፡ ከንቲባ አዳነች በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ72 ሀገሮችና 115 አቻ ከተማ…

ከ1 ሺህ በላይ የቡና አምራች አርሶ አደሮች ምርታቸውን ለውጭ ገበያ እያቀረቡ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ1 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች የላኪነት ፈቃድ በማውጣት የቡና ምርታቸውን በቀጥታ ለውጭ ገበያ እያቀረቡ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ሀገራዊ የቡና ኤግዚቢሽንና የእውቅና መርኃ-ግብር ''ቡናችን…

ፓርቲዎች በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖች ወደ ምክክር መድረኩ እንዲመጡ እገዛ እንዲያደርጉ ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከ45 የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡ የውይይት መድረኩ ፓርቲዎቹ በሀገራዊ ምክክሩ ሊኖራቸው የሚገባውን ሚና እና ተሳትፎ ለማጎልበት ታስቦ የተዘጋጀ ነው ተብሏል፡፡ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር…

ኢትዮጵያና ደቡብ ኮሪያ የ10 ሚሊየን ዶላር የፕሮጀክት ድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ የ10 ሚሊየን ዶላር የፕሮጀክት ድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡ ስምምነቱ የግብርና እና የተቀናበሩ የግብርና ምርት ውጤቶች ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡…