ስፓርት
ሪያል ማድሪድ ዲን ሁይሰንን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ የመሐል ተከላካይ ስፍራ ተጫዋች የሆነውን ዲን ሁይሰንን ከቦርንማውዝ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
ስፔናዊው ተጫዋቹ በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን በእንግሊዙ ክለብ ቦርንማውዝ በነበረው ቆይታ በሊጉ 32 ጨዋታዎችን አድርጎ ሦስት ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፤ ሁለት ግብ የሆኑ ኳሶችንም አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
የ20 ዓመት ወጣቱ የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ዲን ሁይሰን ከቦርንማውዝ አስቀድሞ የጣሊያን ክለቦች በሆኑ ሮማ እና ጁቬንቱስ መጫወቱ ይታወሳል፡፡…
Read More...
ሀዋሳ ከተማ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀዋሳ ከተማ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቢንያም በላይ የሀዋሳ ከተማን ማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።
ረፋድ ላይ በተደረገው ጨዋታ መቐለ 70 እንደርታ እና ኢትዮጵያ ቡና 1…
ሲዳማ ቡና ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሲዳማ ቡና ወላይታ ድቻን በማሸነፍ የ2017 የኢትዮጵያ ዋንጫ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል።
ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 አሸንፏል።
የሲዳማ ቡናን ግቦች ሀብታሙ ታደሰ እና መስፍን ታፈሰ ሲያስቆጥሩ የወላይታ ድቻን ብቸኛ ግብ ካርሎስ ዳምጠው ከመረብ አሳርፏል።…
18ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ሩጫ ውድድር ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) መነሻውንና መድረስ በመስቀል አደባባይ ያደረገው 18ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር በሴቶች ፋንቱ ወርቁ እና በወንዶች ሌሊሳ ፉፋ አሸንፈዋል።
ውድድሩን በሴቶች ፋንቱ ወርቁ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በበላይነት ስታጠናቅቅ÷ ውድድሩን ለመጨረስ 1 ሰዓት ከ13 ደቂቃ 30 ሴኮንድ ወስዶባታል።
በውድድሩ ዓይንዓለም ደስታ ከመቻል…
የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ይደረጋል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ፖርቹጋል ከስፔን ዛሬ ምሽት የሚያደርጉት የፍጻሜ ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል፡፡
ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሙኒክ አሊያንዝ አሬና ስታዲየም የሚደረግ ሲሆን÷ ሁለቱ ቡድኖች ካላቸው ምርጥ ተጫዋቾች አንጻር አጓጊ ሆኗል፡፡
በፖርቹጋል በኩል የ40 ዓመቱ ክሪስቲያኖ ሮናልዶን ጨምሮ ቪቲኒሃ፣ ጆዓዖ ኔቬስ…
ቶተንሀም ሆትስፐር አንጂ ፖስቴኮግሉን አሰናበተ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሀም ሆትስፐር የክለቡን አሰልጣኝ አንጂ ፖስቴኮግሉን አሰናብቷል፡፡
አሰልጣኙ በስፐርስ በነበራቸው የሁለት ዓመት ቆይታ የዩሮፓን ሊግ ዋንጫን አሳክተዋል፡፡
በፖስቴኮግሉ የተመራው ቶተንሀም በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በፕሪሚየር ሊጉ ደካማ የውድድር ጊዜ አሳልፏል፡፡
በሊጉ ካደረጋቸው 38…
ራፊንሀ -የስፔን ላሊጋ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ብራዚላዊው የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና የፊት መስመር ተጫዋች ራፊንሀ የ2024/25 የውድድር ዓመት የስፔን ላሊጋ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል፡፡
ራፊንሀ በውድድር ዘመኑ ለባርሴሎና 36 የላሊጋ ጨዋታዎችን በማድረግ 18 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
እንዲሁም ዘጠኝ ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አማቻችቶ ማቀበል ችሏል፡፡
ባርሴሎና…