Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ የሚገኙ የሚሊተሪ አታሼ ማህበር አባላት ጎብኝት አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የሚገኙ ከ30 ሀገራት በላይ የተውጣጡ የሚሊተሪ አታሼ ማህበር አባላት ዛሬ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል÷ጉብኝቱ ለፖሊስና ለሚሊተሪው የእርስ በርስ የልምድ ልውውጥ…

የሸዋል ኢድ በዓል የቱሪስት መዳረሻነቱን ለማሳደግ በትኩረት እንሰራለን- የሐረሪ ክልል የባህል ቡድን አባላት

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሸዋል ኢድ በዓል የቱሪስት መዳረሻነቱን ለማሳደግ በትኩረት እንሰራለን ሲሉ የ18ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል የተሳተፉ የሐረሪ ክልል የባህል ቡድን አባላት ገለጹ። ሸዋል ኢድ የሐረሪ ህዝብ…

በሰላማዊ ሰልፍ ሽፋን አዲስ አበባን የሁከትና የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች ሴራ መክሸፉን የጋራ ግብረ- ኃይሉ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰላማዊ ሰልፍ ሽፋን አዲስ አበባን የሁከትና የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ የሽብር ተልዕኮ ተቀብለው በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች ሴራ መክሸፉን የጸጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል አስታውቋል፡፡ የጸጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል…

የቡና ግንድ አድርቅ በሽታን መከላከል የሚያስችል መድኃኒት በምርምር ተገኘ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቡና ግንድ አድርቅ በሽታን መከላከል የሚያስችል መድኃኒት በምርምር ማግኘቱን አስታወቀ። ዩኒቨርሲቲው የቡና ግንድ አድርቅ በሽታን በምስራቅ አፍሪካ በምርታማነት ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመከላከል ያለመ…

የአትሌት ድርቤ ወልተጂ የ1 ማይል ርቀት ክብረወሰን ፀደቀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ድርቤ ወልተጂ የአንድ ማይል ርቀት ክብረወሰን በአለምአቀፉ  አትሌቲክስ እውቅና አግኝቷል። ለመጀመሪያ ጊዜ በላቲቪያ ሪጋ በ1 ማይል ርቀት በተካሄደው የሴቶች ውድድር አትሌት ድርቤ ወልተጂ በ4 ደቂቃ ከ20 ሰከንድ ከ98…

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) አክሶን የሕክምና ማእከልን ጎብኙ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አክሶን የሕክምና ማእከልን ጎብኝተዋል፡፡ ማእከሉ ለስትሮክ እና ኒውሮሎጂ ህመም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የፅኑ ህክምና እና እንክብካቤ የሚሰጥ መሆኑን…

የብራዚሉ ክለብ ሳንቶስ ከ111 ዓመት በኋላ ወደ ታችኛው ዲቪዚዮን መውረዱ አነጋጋሪ ሆኗል

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በርካታ ከዋክብቶችን ያፈራው የብራዚሉ ክለብ ሳንቶስ ከ111 ዓመት በኋላ ወደ ታችኛው ዲቪዚዮን መውረዱ ደጋፊዎችን አስቆጥቷል፡፡ ሳንቶስ የክለቡ ወርቃማ ዘመን በተባለው  1950ዎቹ እና 60ዎቹ 12 የሀገራዊ ውድድር ክብሮችን፣6 የሊግ ውድድር…

ዓለም አቀፍ የእርሻና ምግብ የንግድ ትርዒት ተከፈተ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 14ኛው አዲስ ቻምበር ዓለም አቀፍ የእርሻና የምግብ የንግድ ትርዒት በሚሊኒየም አዳራሽ ተከፈተ። የንግድ ትርዒቱ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሕዳር 29 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን÷ ከ70 በላይ ከሀገር ውስጥና ከአውሮፓ፣ ከመካከለኛው ምሥራቅና…

በሲዳማ ክልል ከደረጃ በታች የሆኑ 17 የግል ኮሌጆች መዘጋታቸው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሲዳማ ክልሉ ከደረጃ በታች የሆኑና በህገ-ወጥነት የተገመገሙ 17 የግል ኮሌጆችን ማዘጋቱን የክልሉ ስራ፣ ክህሎትና ኢንተርፕራይዝ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የመንግስት እና የግል ኮሌጆች የ2015 ዓ.ም ክትትልና ግምገማ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓዋል።…