Fana: At a Speed of Life!

በበጀት ዓመቱ 8 የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በያዝነው ዓመት ስምንት የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ክብሮም ካህሳይ እንደገለጹት÷…

ዩክሬን በካርኮቭ ላካሄደችው ዘመቻ አሜሪካ ድጋፍ ማድረጓን ሴናተር ዋርነር አረጋገጡ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሩሲያ - ዩክሬን ጦርነት ዩክሬን ከሰሞኑ ባደረገችው የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ ለተገኘው “ሥኬት” አሜሪካ እና አጋሮቿ ድጋፍ ማድረጋቸው ተገለጸ፡፡ አሜሪካ እና አጋሮቿ የሆኑት የሰሜን ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) አባል ሀገራት ዩክሬን በካርኮቭ…

በቢሾፍቱ በ133 ሚሊየን ብር የተቋቋመው ፋብሪካ ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቢሾፍቱ ከተማ በ133 ሚሊየን ብር የተቋቋመው ጀብዱ ሞተርስ አክሲዮን ማህበር የግብርና መሳሪያዎች መገጣጠሚያ እና ማምረቻ ፋብሪካ ተመረቀ። ፋብሪካው ለመስኖ ልማት የሚያግዙ የውሃ መሳቢያ (ፓምፕን) ጨምሮ ለግብርና ምርት አጋዥ የሆኑ የግብርና…

በሰቆጣ ግንባር ለተሠለፈው ጥምር ጦር ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዋግኽምራ ዞን የደሃና ወረዳ እና የአምደ ወርቅ ከተማ አስተዳደር 785 ሺህ ብር የሚገመት የቁም እንስሳት በሠቆጣ ግንባር ለተሠለፈው ጥምር ጦር አበርክተዋል፡፡ ድጋፉን ያስረከቡት የደሃና ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ዘነበ ማሞ÷ ለኢትዮጵያ…

ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ የፊፋ የቴክኒክ ባለሙያ ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የባህርዳር ከነማ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ የፊፋ የቴክኒክ ባለሙያ ሆነው ተሾመዋል። አሰልጣኙ ፊፋ ለቴክኒክ ባለሙያነት ያቀረባቸውን መመዘኛዎች በማለፍ እንደ ሁኔታው በሚታደስ የሁለት ዓመት ኮንትራት የፊፋ የቴክኒክ ባለሙያ ሆነዋል።…

የኩላሊት እጥበት ለማድረግ አቅማቸው ለማይፈቅድ የመዲናዋ ነዋሪዎች 20 ሚሊየን ብር ተመደበ 

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2015 በጀት ዓመትከፍለው የኩላሊት እጥበት ማድረግ ለማይችሉ ዜጎች 20 ሚሊየን ብር መመደቡን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዳግማዊ ምኒሊክ ሆስፒታል በመንግስትና የግል ሴክተሩ አጋርነት የኩላሊት…

ቴድሮስ አድኀኖም ለህወሓት ድምጽ በመሆን ሲሰራ ቆይቷል – ጋዜጠኛ አልስተር ቶምሰን

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድኀኖም የአሸባሪው የህወሓት ቡድን አፈ-ቀላጤ ሆኖ የመረጃ ጦርነቱን ሲመራ መቆየቱን ኒውዝላንዳዊው ጋዜጠኛ አልስተር ቶምሰን ገለጸ፡፡ አልስተር ቶምሰን ስኩፕ ሚዲያን ከመሰረቱት ጋዜጠኞች አንዱ ሲሆን…

ለመከላከያ ሠራዊትና በጎርፍ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚደረገው ድጋፍ ይቀጥላል- አቶ ኡሞድ ኡጁሉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በግንባር ለተሰለፉ የመከላከያ ሠራዊትና በክልሉ በጎርፍ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ ገለፁ። አቶ ኡሞድ ኡጁሉ እንደገለጹት÷ የአሸባሪው ህወሓት ሀገር የማፍረስ ሴራ…

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዙሪክ-ሚላን አዲስ አበባ በረራ ሊጀምር ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዙሪክ-ሚላን አዲስ አበባ ከጥቅምት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በረራ እንደሚጀምር ተገልጿል። አየር መንገዱ በሳምንት ሶስት ጊዜ ከስዊዘርላንድ ዙሪክ በመነሳት በጣልያን ሚላን ወደ አዲስ አበባ በረራ እንደሚያደርግ…

በቀጣዮቹ 10 ቀናት በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች የዝናብ ስርጭቱ ይቀጥላል- ኢንስቲትዩቱ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብና በደቡብ ምዕራብ የኢትዮጵያ ክፍል ዝናቡ ቀጣይነት እንደሚኖረው የኢትዮጵያ ሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ ደቡባዊ የሀገሪቱ አካባቢዎችም ሁለተኛውን የዝናብ ወቅታቸውን ቀስ በቀስ ያገኛሉ የተባለ ሲሆን፥ በአንጻሩ በሰሜንና በሰሜን…