Fana: At a Speed of Life!

ወደ ግብር ከፋይ ሰንሰለት ያልገቡ አካላትን ሕጋዊ መስመር ለማስያዝ እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ወደ ግብር ከፋይ ሰንሰለት ያልገቡ አካላትን ወደ ሕጋዊ ሥርዓት ለማስገባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሀገራዊ እና በገቢ ዘርፍ…

ኢትዮጵያና ፓኪስታን በሠላምና ደህንነት ዘርፎች በትብብር ለመስራት መከሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) ከፓኪስታን የሀገር ውስጥና አደንዛዥ እፅ ቁጥጥር ሚኒስትር ሰይድ ሞሀሲን ናክቪ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም የሀገራቱን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ትብብር ማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች…

በትግራይ ክልል ተቋርጦ የቆየው የቀድሞ ታጣቂዎች የተሃድሶና መልሶ ማቋቋም ስልጠና ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በትግራይ ክልል ተቋርጦ የቆየው የቀድሞ ታጣቂዎች የተሃድሶና መልሶ ማቋቋም ስልጠና ዳግም ተጀምሯል። የአፍሪካ ሕብረትና የዓለም አቀፍ ተቋማት ታዛቢዎችና ተወካዮች ለቀድሞ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች የሚሰጠውን የተሃድሶና መልሶ ማቋቋም የስልጠና ሒደት…

ኢትዮጵያ እና ኬንያ የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳለጥ የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እና ኬንያ የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳለጥ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ÷ ትናንት የተጀመረው የኢትዮ-ኬንያ የድንበር ላይ ንግድ…

የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ መሻሻል ሚዲያዎች በኃላፊነት እንዲንቀሳቀሱ ያግዛል – ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ መሻሻል ሚዲያዎች በኃላፊነት እንዲንቀሳቀሱና ለሀገር ግንባታ የሚኖራቸውን ድርሻ ይበልጥ ከፍ እንዲያደርጉ የሚያግዝ መሆኑን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) ገለጹ። 6ኛው…

ኢትዮጵያ 5ኛውን የፒ4ጂ ጉባኤ ለማዘጋጀት ችቦውን በመረከቧ ኩራት ይሰማታል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በ2027 የሚካሄደውን አምስተኛውን የፒ4ጂ ጉባኤ ለማዘጋጀት ችቦውን በመረከቧ ኩራት ይሰማታል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ÷ የሀኖይ ጉባኤ አነስተኛ…

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት አዋጆችን አፀደቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ስብሰባው ሁለት ረቂቅ አዋጆች ላይ ተወያይቶ አፅድቋል። ምክር ቤቱ ካፀደቃቸው አዋጆች መካከል የመገናኛ ብዙሃን አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅ የመጀመሪያው ሲሆን÷…

ጸሎተ ሐሙስ ሥነ ሥርዓት በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጸሎተ ሐሙስ ሥነ ሥርዓት በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እየተከናወነ ነው። በአዲስ አበባ ሀገረስብከት ልደታ ማርያም ካቴድራል ቤተክርስቲያን የሥነ ሥርዓቱ አካል የሆነው መስዋዕተ ቅዳሴ እየተካሄደ ይገኛል። በቤተክርስቲያኒቱ ጸሎተ ሐሙስ…

ባለፉት 9 ወራት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስከበሩ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል – አምባሳደር ነብያት ጌታቸው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት ዘጠኝ ወራት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስከበሩ ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው አስታወቀ። አምባሳደር ነብያት በሰጡት መግለጫ÷ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በፖለቲካና ኢኮኖሚ ዘርፎች…

የጸሎተ ሐሙስ ሥነ-ሥርዓት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጸሎተ ሐሙስ ሥነ-ሥርዓተ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል እየተከናወነ ነው፡፡ በሥነ-ሥርዓቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ጨምሮ ሊቃነ…