ስፓርት
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሰባት ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ12ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ሰባት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
ቀን 9 ሰዓት 30 ላይ ቼልሲ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ በርንሌይን በሚገጥምበት ጨዋታ 12ኛ ሳምንት የሊጉ ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራሉ፡፡
በ20 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ቼልሲ በሊጉ ተከታታይ 3ኛ ጨዋታውን ድል ለማድረግ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ባለሜዳው በርንሌይ በበኩሉ በሊጉ ከሁለት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በሌላ የሊጉ ጨዋታ ምሽት 12…
Read More...
ተስፋ ያላቸው አዳጊዎች ወደ እግር ኳሳችን እየመጡ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀትና አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን ለመገንባት ተስፋ ያላቸው አዳጊዎች ወደ እግር ኳሳችን እየመጡ ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ተገኝተው በሴካፋ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ከ17…
ኢትዮጵያ ሁለተኛ የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ19ኛው የአፍሪካ ብስክሌት ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ሁለተኛ የወርቅ ሜዳሊያ አስመዝግባለች።
64 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በሸፈነው የአዳጊ ወጣቶች የጎዳና ላይ ውድድር፣ በሴቶች ብስክሌተኛ ፅጌ ካህሳይ ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቃለች።
ፅጌ ካህሳይ ትላንት በተደረገው የግል ሰዓት ሙከራ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ ማሸነፏ ይታወቃል።…
ከ28 ዓመታት በኋላ ወደ ዓለም ዋንጫ ያለፉ ብሔራዊ ቡድኖች…
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ28 ዓመታት ጥበቃ በኋላ ወደ ትልቁ መድረክ የዓለም ዋንጫ ሦስት ብሔራዊ ቡድኖች አልፈዋል፡፡
ኖርዌይ፣ ስኮትላንድ እና ኦስትሪያ ከ28 ዓመታት ጥበቃ በኋላ ወደ ዓለም ዋንጫ ያለፉ ሀገራት ናቸው፡፡
ኖርዌይ ለመጨረሻ ጊዜ በዓለም ዋንጫ የተሳተፈችው በፈረንጆቹ 1998 በፈረንሳይ አስተናጋጅነት በተካሄደው የዓለም ዋንጫ…
ፈርናንዲንሆ ራሱን ከእግር ኳሱ ዓለም አገለለ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቀድሞ የማንቼስተር ሲቲ ተጫዋች ፈርናንዲንሆ ራሱን ከእግር ኳሱ ዓለም ማግለሉን ይፋ አድርጓል።
ብራዚላዊው የቀድሞ የማንቼስተር ሲቲ ተጫዋች ፈርናንዲንሆ በ40 ዓመቱ ነው ጫማውን የሰቀለው።
ፈርናንዲንሆ በእግር ኳስ ሕይወቱ አምስት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን ጨምሮ የተለያዩ ዋንጫዎችን አሳክቷል።
ፈርናንዲንሆ ጫማ…
የአውሮፓ ሀገራት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ጥሎ ማለፍ ድልድል ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሀገራት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ጥሎ ማለፍ ድልድል ይፋ ሆኗል፡፡
በዚህም መሠረት በምድብ አንድ ጣሊያን ከ ሰሜን አየርላንድ እንዲሁም ዌልስ ከ ቦስኒያ ተደልድለዋል።
በምድብ ሁለት ዩክሬን ከስዊድን እንዲሁም ፖላንድ ከአልባኒያ ተገናኝተዋል።
በምድብ ሦስት ቱርክ ከ ሮማኒያ እንዲሁም ስሎቫኪያ ከኮሶቮ…
ኢትዮጵያ በአትሌቲክሱ ዘርፍ ሁለት እውቅናዎችን አገኘች
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በአትሌቲክስ ዘርፍ ሁለት እውቅናዎችን ከዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማሕበር አገኘች።
ኢትዮጵያ እውቅናውን ያገኘችው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ እና አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ ለነበረው ሚና እንደሆነ ተገልጿል።
የእውቅና ሥነ ሥርዓቱ በብሔራዊ ሙዚዬም የተከናወነ ሲሆን÷ ስፖርት ለቱሪዝም ዘርፉ መነቃቃት ወሳኝ ሚና…