Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

የስፖርት ዘርፉን ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው – አቶ አወሉ አብዲ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወሉ አብዲ የስፖርት ዘርፉን ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው አሉ፡፡ 20ኛው የኦሮሚያ ስፖርት ምክር ቤት ጉባዔ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ አቶ አወሉ አብዲ በመድረኩ እንዳሉት÷ እንደ ሀገር ለስፖርት ዘርፉ የተሰጠውን ትኩረት ተከትሎ የክልሉ መንግስት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ለማስፋፋት በሰራቸው ስራዎች ስኬቶች ተመዝግበዋል። በኢትዮጵያ ትልቅ እና የስፖርት ዘርፍ ምልክት የሆነው አትሌቲክስ ዳግም እንዲያንሰራራ…
Read More...

በ25 ዓመቱ 27 ሀትሪክ የሰራው ሃላንድ…

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25 ዓመቱ 27 ሀትሪክ የሰራው የማንቼስተር ሲቲው የፊት መስመር ተጫዋች ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ፡፡ የሲቲው የፊት መስመር ተጫዋች ሃላንድ አሁን ላይ በአጠቃላይ በእግር ኳስ ሕይወቱ ከዕድሜው ቁጥር በላይ ሀትሪክ በመስራት የራሱን ደማቅ ታሪክ እየጻፈ ይገኛል፡፡ በዓለም ላይ ካሉ ምርጥ የፊት መስመር ተጫዋቾች አንዱ…

ዲዮንግ በባርሴሎና ለተጨማሪ አምስት ዓመታት የሚያቆየውን ስምምነት ፈረመ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የባርሴሎናው አማካይ ቦታ ተጨዋች ፍሬንኪ ዲዮንግ በክለቡ ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚያቆየውን አዲስ ኮንትራት መፈረሙ ይፋ ተደርጓል። በ2019 ከአያክስ የካታሎኑን ቡድን ባርሴሎና የተቀላቀለው ፍሬንኪ ዲዮንግ በቡድኑ የአማካይ ቦታ ላይ ድንቅ እንቅስቃሴን ሲያሳይ ቆይቷል። እስከ 2029 ድረስ የሚያቆየውንን አዲስ ውል…

አትሌት ታምራት ቶላ  ከአምስተርዳም  ማራቶን ውድድር ውጪ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ34 ዓመቱ አትሌት ታምራት ቶላ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ከ50ኛው የአምስተርዳም ማራቶን ውድድር ውጪ ሆኗል። ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳረጋገጠው፤ የአምስተርዳም ማራቶን ክብረ ወሰን ባለቤት አትሌት ታምራት ቶላ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ነው ከውድድሩ ውጪ የሆነው። የኦሊምፒክ እና የዓለም ሻምፒዮን ባለድሉ አትሌት…

ስዊድን አሰልጣኟን አሰናበተች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሰልጣኝ ጆን ዳህል ቶማሰን ከስዊድን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነታቸው ተሰናበቱ፡፡ የስዊድን ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ እያስመዘገበ የሚገኘውን ውጤት ተከትሎ ነው ዋና አሰልጣኙን ያሰናበተው፡፡ ስዊድን በ2026 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ካደረገቻቸው አራት ጨዋታዎች በሦስቱ ተሸንፋ በአንዱ አቻ ተለያይታለች፡፡…

ሌዋንዶውስኪ ከኤልክላሲኮ ጨዋታ ውጪ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሮበርት ሌዋንዶውስኪ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ከኤልክላሲኮ ጨዋታ ውጪ ሆኗል፡፡ የ37 ዓመቱ የባርሴሎናው የፊት መስመር ተጫዋች የጡንቻ ጉዳት እንዳጋጠመው ነው የተገለጸው፡፡ ሌዋንዶውስኪ ባጋጠመው ጉዳት ከአራት እስከ ስድስት ሳምንታት ከሜዳው ሊርቅ እንደሚችል እየተዘገበ ይገኛል፡፡ በ10ኛ ሳምንት የስፔን ላሊጋ መርሐ…

በቺካጎ ማራቶን ሃዊ ፈይሳ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ47ኛው የቺካጎ ማራቶን አትሌት ሀዊ ፈይሳ አሸንፋለች፡፡ አትሌት ሀዊ ፈይሳ ርቀቱን 2 ሰዓት 14 ደቂቃ ከ56 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ቀዳሚ የሆነችው፡፡ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት መገርቱ አለሙ ደግሞ 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች፡፡