Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

የሀገር ውስጥ ዜና

ጥምቀትን በጎንደር ለማክበር የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት እየተደረገ ነው

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በመጪው ጥር ወር የሚከበረውን የጥምቀት በዓል በጎንደር ለማክበር የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት እየተደረገ ነው የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኛው፡፡ አቶ ቻላቸው ዳኛው ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ ወርሃ ጥር…

በክልሉ ጥንታዊ ቅርሶች ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ በትኩረት እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል ጥንታዊ ቅርሶች ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ፡፡ የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ የቁጥጥርና አሠሪ ኮሚቴዎችና የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሙያዎችን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት…

ኢትዮጵያ በስትራቴጂ የሚመራ ዘላቂ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሰራች ነው – ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በስትራቴጂ የሚመራ ዘላቂ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሰራች ነው አሉ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፡፡ በኢትዮጵያ ብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ 2025 ኤግዚቢሽን እና ፎረም በዛሬው እለት ምክትል ጠቅላይ…

የኢትዮጵያ ብልፅግና አረንጓዴ ኢኮኖሚን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብልጽግና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን እየተሰራ ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ። በኢትዮጵያ ብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ 2025 ኤግዚቢሽን እና ፎረም ተጀምሯል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ…

 ጉምሩክ ኮሚሽን ከመደኛ ስራው በተጨማሪ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል – ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተቋሙ ከመደበኛ ስራው በተጨማሪ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል አሉ። የኮሚሽኑ ጅግጅጋ ቅርንጫፍ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ያስገነባውን የሼህ አሊ ጉሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዛሬው እለት…

የቻይና-ኢትዮጵያ የቡና ኢኮኖሚና ንግድ ትብብር ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቻይና-ኢትዮጵያ የቡና ኢኮኖሚና ንግድ ትብብር ኮንፈረንስ በቻይና ሁናን ግዛት ጁጆ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው ኮንፈረንሱ የኢትዮጵያን ቡና በቻይና ይበልጥ ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ በዚህ ወቅት…

ግብጽ ደቡብ አፍሪካን አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታ ዛሬ ቀጥሎ ሲካሄድ ግብጽ ደቡብ አፍሪካን 1 ለ 0 አሸንፋለች። ምሽት 12 ሰዓት በተደረገው ጨዋታ ግብጽ መሐመድ ሳላህ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠራት ግብ ሶስት ነጥብ ይዛ…

የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ። ላለፉት ሁለት ቀናት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በመምከር ሲካሄድ የቆየው የምክር ቤቱ 11ኛ መደበኛ ጉባኤ፤ በዛሬው ዕለት በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ የቀረቡ…

የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ፖሊሲ የዲጂታል ሥራ ፈጠራን የሚደግፍ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢንተርፕረነርሽፕ ልማት ፖሊሲ ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ተጣጣሚ በሆነ መልኩ የዲጂታል ሥራ ፈጠራንና ተወዳዳሪነትን የሚደግፍ ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር…

18 ዓመት ያልሞላቸውን ልጆች ወደ አውሮፓ እልካችኋለሁ በማለት ገንዘብ የተቀበለው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እድሜያቸው 18 ዓመት ያልሞላ 5 ልጆችን ለስራ ስምሪት ወደ አውሮፓ ሀገራት እልካችኋለሁ በማለት ገንዘብ ሲቀበል የነበረ ግለሰብ በ12 ዓመት ፅኑ እስራት እና በገንዘብ ተቀጣ። የቅጣት ውሳኔውን ያሳለፈው በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት…