Fana: At a Speed of Life!

የከተራና ጥምቀት በዓል በሰላም እንዲከበር ወደ ሥራ መግባቱን ግብረ-ኃይሉ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2016 ዓ.ም የከተራና ጥምቀት በዓል በሰላም እንዲከበር ዕቅድ አውጥቶ ወደ ሥራ መግባቱን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታውቋል፡፡ የከተራና ጥምቀት በዓል በሰላም እንዲከበር የፀጥታ አካላት ዝግጅታቸውን አጠናቀው ወደ ሥራ መግባታቸውንም…

በሀሰተኛ ሰነዶች ግለሰቦች ሳያውቁ ቤታቸውን ለመሸጥ ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የተቀበለው ተከሳሽ በእስራትና በገንዘብ ተቀጣ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ሀሰተኛ ሰነዶችን በመጠቀም ግለሰቦች ሳያውቁ ቤታቸውን ለመሸጥ ከ15 ሚሊየን ብር በላይ ተቀብሏል የተባለው ተከሳሽ በጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት ወሰነ። በአ/አ ከተማ ኮልፌ…

የጥምቀትን በዓል ለማክበር ዝግጅት መደረጉን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጥምቀትን በዓል ለማክበር ዝግጅት መደረጉን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስታውቋል፡፡ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ በዓሉን አስመልክቶ መግለጫ እየሰጡ ነው፡፡ ብፁዕነታቸው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከጃን ሜዳ በተጨማሪ ከ78…

አምባሳደር ምስጋኑ በ19ኛው በናም ሚኒስትሮች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በ19ኛው የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (ናም) ሚኒስትሮች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ነው፡፡ ጉባኤው ዛሬ ማለዳ በኡጋንዳ ካምፓላ መጀመሩን በኡጋንዳ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ…

“ቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን” ድጋፉን እንዲያጠናክር ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) “ቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን” በኢትዮጵያ እያደረገ ያለውን የልማት ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ፡፡ በዳቮስ እየተካሄደ ከሚገኘው የዓለም የኢኮኖሚ ፎረም ጎን ለጎን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከ“ቢል…

በመዲናዋ ቆሻሻን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ከ746 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኘ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሥድስት ወራት ቆሻሻን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ከ746 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱ ተገለጸ፡፡ ገቢው የተገኘው 44 ሺህ ቶን ቆሻሻን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል መሆኑን የአዲስ አበባ ፅዳት አሥተዳደር…

የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ከሶማሊላንድ ጋር የተደረሰውን ስምምነት እንደሚደግፍ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት በኢትዮጵያና ሶማሊላንድ መካከል የተፈረመውም የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት እንደሚደግፍ አስታውቋል። የምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት ፉአድ ገና ስምምነቱን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ ምክር ቤቱ የወጣቶችን…

ኳታርና ፈረንሣይ በጋዛ ለታጋቾች መድሃኒት መላከቸው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኳታር እና ፈረንሣይ በጋዛ ለሚገኙ ታጋቾች መድኃኒት መላካቸው ተገልጿል። በፈረንጆቹ ህዳር ወር ለሳምንት የቆየው የተኩስ አቁም ስምምነት ካበቃ በኋላ ኳታርና ፈረንሳይ ከእስራኤል እና የሃማስ ታጣቂ ቡድን ጋር በደረሱት ስምምነት በጋዛ…

የ78 ዓመት ወላጅ እናቱን የገደለው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ78 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ወላጅ እናቱን የገደለው ተከሳሽ በጽኑ እሥራት መቀጣቱን ፍትሕ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ አዲስ አስራት ይመር የተባለው ተከሳሽ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ደብረሰላም ትምህርት ቤት አካባቢ ከ78 ዓመት ወላጅ እናቱ ጋር ይኖር…

የአርብቶ አደሮችን ተጠቃሚነት የሚያጠናክሩ ሥራዎች በቀጣናው እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የምሥራቅ አፍሪካ አርብቶ አደሮችን የጋራ ተጠቃሚነትና ትስስር የሚያጠናክሩ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ኢትዮጵያ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ በየሁለት ዓመቱ የሚከናወን ሀገር አቀፍ የአርብቶ አደሮች ቀን በማክበር…