Fana: At a Speed of Life!

በጤና ተቋማት የሚወልዱ እናቶች ቁጥር 74 በመቶ መድረሱ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በጤና ተቋማት የወሊድ አገልግሎት ያገኙ እናቶችን 74 በመቶ ማድረስ መቻሉን የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ገለፁ፡፡ የሴቶች የልማት ህብረት አደረጃጀትን ለማጠናከር ያለመ ውይይት የጤና ሚኒስትሯ  ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ የሴቶችና…

በደብረ ማርቆስ ከተማ የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በደብረ ማርቆስ ከተማ በወቅታዊ የሰላምና ጸጥታ ዙሪያ የሚመክር ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው፡፡ ኮንፈረንሱ “ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም” በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው፡፡ በመድረኩ በከተማ አስተዳደሩ ከአራቱም ክፍለ ከተሞች…

የውኃ ሀብታችንን በብቃት ስንመራ የጎረቤት ሀገራትን ጭምር ብልጽግና የምንደግፍበት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የውኃ ሀብታችንን ስንጠብቅና በብቃት ስንመራ የኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የጎረቤት ሀገራትን ጭምር መረጋጋትና ብልጽግና የምንደግፍበት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ያዘጋጀው…

የኃይማኖት ተቋማት ፅንፈኝነትና የመከፋፈል እሳቤን ለማስወገድ በቁርጠኝነት መስራት አለባቸው – ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኃይማኖት ተቋማት ለዓለም ፈተና እየሆነ ያለውን የፅንፈኝነትና የመከፋፈል እሳቤን ለማስወገድ በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ተናገሩ። የሰላም ሚኒስቴር በተባባሩት አረብ ኢምሬቶች ከሚገኘው ከመሐመድ ቢን…

ኢትዮጵያ ታዳጊ ሀገራት ፍላጎታቸውን ያማከለ ውክልና በተመድ ውስጥ ሊኖራቸው እንደሚገባ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ታዳጊ ሀገራት ፍላጎታቸውን ያማከለ ውክልና በተባበሩት መንግስታት ድርጀት (ተመድ) ውስጥ ሊኖራቸው እንደሚገባ ኢትዮጵያ አስገነዘበች። ኢትዮጵያ በሩሲያ ካዛን ከተማ የተካሄደውን 16ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ውጤት አስመልክቶ ጀኔቫ የሩሲ…

በአማራ ክልል ከመስኖ ልማት 47 ሚሊየን ኩንታል ምርት ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በ2017 ዓ.ም በመስኖ ከሚለማው እርሻ 47 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታስቦ ወደ ተግባር መገባቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡ ክልሉ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ የማልማት አቅም እንዳለው ቢታመንም…

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሩብ ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ማካሄድ ተጀምሯል። በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሃሰን እና የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር…

በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) "ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ሀሳብ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች በገጠሙት የፀጥታ ችግሮች ዙሪያ የሚመክር የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው፡፡ በደባርቅ ከተማ ወቅታዊውን የጸጥታ ሁኔታ በሚመለከት ከከተማው ወጣቶች ጋር ውይይት…

5ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ማጠቃለያ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) 5ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ማጠቃለያ መርሐ-ግብር በድሬዳዋ አስተዳደር እየተካሄደ ነው ፡፡ መርሐ ግብሩ "የቁልፍ መሰረተ ልማት ደህንነት ለዲጂታል ሉዓላዊነት በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው፡፡ በመድረኩ የድሬዳዋ…

ጠንክረን ከሠራን በአካባቢያችን ተዓምር መሥራት እንደሚቻል ተገንዝበናል – አቶ አወል አርባ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አወል አርባ በገቢ ረሱ ሐንሩካ ወረዳ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝታቸውም በሀንሩካ ወረዳ እየለማ የሚገኘውን የሙዝ ማሳ ጨምሮ ሌሎች የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡…