Fana: At a Speed of Life!

ምክር ቤቱ በጎፋ የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰ የመሬት መንሸራተት ምክንያት ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚውል 5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል…

የተለያዩ ተቋማት ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ተቋማት ‘የምትተክል ሀገር፤ የሚያጸና ትውልድ’ በሚል መሪ ሀሳብ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራሮችና ሠራተኞች በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ…

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ትውልድ የመገንባት ሚናን እየተወጣ ያለ ተቋም ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በሀገሪቱ ሁለንተናዊ ታሪክ፣ እድገትና ትውልድ የመቅረጽ ጉልህ ሚና የነበረውና ይህን አጠናክሮ እየቀጠለ ያለ ተቋም እንደሆነ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መሀመድ እድሪስ ገለጹ። ድርጅቱ "ብላቴናት"…

አቶ ሽመልስ አብዲሳ በሊበን ወረዳ የስንዴ ሰብል ምርት ማሰባሰብ ስራን አስጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በክልሉ ምስራቅ ቦረና ዞን ሊበን ወረዳ የለማውን የስንዴ ሰብል ምርት ማሰባሰብ ስራ አስጀመሩ። አቶ ሽመልስ አብዲሳ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ አካባቢው በሚያጋጥመው ተደጋጋሚ ድርቅ በሴፍቲኔት…

በኢንዱስትሪዎች የሚደረጉ ልምምዶች ሰልጣኞች ብቁ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያደርጋል – ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢንዱስትሪዎች የሚደረጉ ልምምዶች ሰልጣኞች ተጨባጭ እውቀትና ክህሎት ይዘው እንዲወጡ ከማድረግ ባሻገር ብቁ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያደርጋል ሲሉ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለጹ፡፡ የከፍተኛ ትምህርት፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና፣ የምርምር…

የፌደራል ፖሊስ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሥራ ሃፊዎችና አባላት ኮልፌ በሚገኘው የልዩ ፀረ ሽብር መምሪያ ግቢ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል÷ ፖሊስ በተለያዩ ጊዜያት ከህብረተሰቡ ጎን በመሆን…

የወባ በሽታ ስርጭትን በዘላቂነት ለመግታት የከፍተኛ አመራሮች የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የወባ በሽታ ስርጭትን በዘላቂነት ለመግታት የከፍተኛ አመራሮች የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል፡፡ መድረኩን ጤና ሚኒስቴር ከመከላከያ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እንዳዛጁት የተገለጸ ሲሆን÷ የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ተቋማቱ ከዚህ በፊትም…

ገቢን ማሳደግ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አንኳር ጉዳይ በመሆኑ ኢኮኖሚው በሚያመነጨው ልክ ገቢ መሰብሰብ አለበት ተባለ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገር ውስጥ ገቢን ማሳደግ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አንኳር ጉዳይ በመሆኑ ኢኮኖሚው በሚያመነጨው ልክ ገቢ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ተናገሩ። የገቢዎች ሚኒስቴር ከከፍተኛ ግብር ከፋዮች ጋር ውይይት እያደረገ ይገኛል።…

መንግሥት ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራ የገባው በበቂ ዝግጅት ነው – ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግሥት ቀጣይነት ያለው እድገት ለማስመዝገብና የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በማለም የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራ የጀመረው በጥናት ላይ የተመሰረተ በቂ ዝግጅት አድርጎ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ።…

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቱርኪዬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቱርኪዬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን ጋር ተወያዩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዛሬ ጠዋት የቱርኪዬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳንን ተቀብዬ አነጋግሬያለሁ…