Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት አባል ሆና ተመረጠች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት አባል ሆና መመረጧን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። ዛሬ በተጀመረው 46ኛው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በተካሄደው ምርጫ ነው ኢትዮጵያ የአፍሪካ…

የጤና ፖሊሲ ማሻሻያ በማድረግ በሽታን ቀድሞ የመከላከል አቅምን ማሳደግ መቻሉ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አካታችነትን ማዕከል ያደረገ የጤና ፖሊሲ ማሻሻያ በማድረግ በሽታን ቀድሞ የመከላከልና አክሞ የማዳን አቅምን ማሳደግ መቻሉን የብልጽግና ፓርቲ ም/ቤት አባልና የጤና ሚኒስትር ዴዔታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ገለጹ፡፡ ዶ/ር ደረጄ የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ…

ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) ከሞሮኮ እና ቱኒዚያ አቻቸው ጋር መከሩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) ከሞሮኮ ውጭ ጉዳይ እና አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር ናስር ቦሪታ እና ከቱኒዚያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሞሀመድ አሊ ናፍቲ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሚኒስትሩ በዛሬው እለት ከተጀመረው 46ኛው የአፍሪካ ሕብረት…

ኢትዮ-ቴሌኮም 61 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮ-ቴሌኮም በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት 61 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ገልጿል፡፡ የኢትዮ-ቴሌኮም ስራ አስፈፃሚ ፍሬ-ሕይወት ታምሩ ÷ በኔትወርክ ማስፋፊያ፣ በአገልግሎት ጥራት፣ አዳዲስ አገልግሎቶችን በማስጀመር…

ካይ ሀቨርትዝ ከውድድር አመቱ ውጪ ሊሆን እንደሚችል ተነገረ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017(ኤፍ ኤም ሲ) ጀርመናዊው የአርሰናል አጥቂ ካይ ሀቨርትዝ በጡንቻ መሸማቀቅ ጉዳት ከውድድር አመቱ  ውጪ ሊሆን እንደሚችል ተነገረ፡፡ ልምምድ ለማድረግ ከክለቡ ጋር ወደ ዱባይ ያመራው ሀቨርትዝ በልምምድ ላይ ባጋጠመው የጡንቻ መሸማቀቅ  ጉዳት አስከውድድር አመቱ…

ጆርዳን ፍልስጤማውያንን ለመቀበል ተስማማች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጆርዳን በአሜሪካ የቀረበላትን ጥያቄ ተከትሎ ከጋዛ የሚመጡ ፍልስጤማውያንን ለመቀበል መስማማቷ ተሰምቷል፡፡ ጆርዳን ፈቃድኝነቷን የገለፀችው የሀገሪቱ መሪ ንጉስ አብዱላሂ ሁለተኛ ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት…

ሳይፈቀድላቸው ድሮን በሚያስነሱ አካላት በጸረ-ድሮን ቴክኖሎጂ ርምጃ እየተወሰደ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017(ኤፍ ኤም ሲ) ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፈቃድ ሳያገኙ በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ድሮን በሚያስነሱና በሚያበሩ አካላት ላይ ርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ የድሮንና ሌሎች በራሪ አካላት…

ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን ለመቋቋም አፍሪካዊ አንድነትን ማጠናከር አለብን – ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017(ኤፍ ኤም ሲ) እያጋጠሙ ያሉ ዘርፈ ብዙ ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን ለመቋቋም አፍሪካዊ አንድነትን አጠናክረን መቀጠል አለብን ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴቲስ (ዶ/ር) ተናገሩ። በ46ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ላይ…

የሕብረቱ ተቋማዊ ሪፎርም መሰረታዊ ለውጥ በሚያመጣ መልኩ እየተከናወነ ነው – ሙሳ ፋኪ ማህማት

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017(ኤፍ ኤም ሲ) የአፍሪካ ሕብረት ተቋማዊ ሪፎርም መሰረታዊ ለውጥ በሚያመጣ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሙሳ ፋኪ ማህማት ገለጹ። 46ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ እየተካሄደ ነው። ሊቀ መንበሩ…

አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን እውን ለማድረግ ያለቪዛ ጉዞን መተግበር እንደሚገባ ተመላከተ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2017(ኤፍ ኤም ሲ) ከቪዛ-ነጻ እንቅስቃሴ ለአፍሪካ ትራንስፎርሜሽን በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ያተኮረ የሚኒስትሮች ስትራቴጂካዊ ውይይት ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌን (ዶ/ር) ጨምሮ ከአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የተለያዩ ባለድርሻ…