Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ ለተከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች መንግሥት 11 ቢሊየን ብር መድቦ እየሠራ ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ለተከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች መንግሥት 11 ቢሊየን ብር ወጭ በማድረግ የረድዔት ሥራዎችን እየሠራ መሆኑን የአደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) ለፋና ብሮድካስቲንግ…

የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት የዓድዋ ሙዚየምን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር አባላት የዓድዋ ሙዚየምን ጎብኝተዋል፡፡ ሙዚየሙ የዓድዋ ድል ጽንስ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ ከተማ ታሪኩን የሚዘክሩ ሁነቶችንና እውነቶችን አካትቶ እየተገነባ የሚገኝ ፕሮጀክት ነው፡፡ በጉብኝቱ…

የ5 ነጥብ 13 ቢሊየን ብር ፕሮጀክት ግንባታ ስምምነት ውል ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ከደቡብ ኮሪያ ሃንሶል ፔፐር ኃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ጋር በ5 ነጥብ 13 ቢሊየን ብር የአደዓ በቾ የከርሰ ምድር ውሃ መስኖ ልማትና የገጠር ልማት ፕሮጀክት ግንባታ ስምምነት ውል ተፈራርሟል፡፡ ፕሮጀክቱ በኦሮሚያ…

ከጥራጥሬና ቅባት እህሎች 159 ሚሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት አራት ወራት ከ184 ሺህ ቶን በላይ የጥራጥሬና የቅባት እህሎች ለውጭ ገበያ በማቅረብ 159 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ እንዳስታወቀው÷ የጥራጥሬና የቅባት እህሎችን ወጪ ንግድ…

በቡና ወጪንግድ ለመሰማራት ፍላጎት ላሳዩ የቻይና ባለሐብቶች ገለፃ ተደረገ

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣስ 10 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቡና ወጪ ንግድ ለመሰማራት ፍላጎት ላሳዩ የቻይና ባለሐብቶች ገለፃ ተደረገላቸው፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ-ግብሩ የቻይና የመንግሥት እና የንግዱ ማኅበረሰብ ቡድን አባላት ተሳትፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቡና ላኪ ድርጅቶች እና የኢትዮጵያ ቡናና…

ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ በኩዌት ኤሚር ህልፈት ሀዘናቸውን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ በኩዌት ኤሚር ናዋፍ አል-አሕመድ አል-ሳባህ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ፡፡ ፕሬዚዳንቷ የኩዌት ኤሚር ሼኽ ናዋፍ አል አሕማድ አል ሳባህ ከዚህ ዓለም በሞት መለየትን አስመልክቶ ለተኳቸው ለኤሚር ሼኽ መሻል አል…

ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነቷን ማረጋገጥ የሚያስችሉ አማራጮች አሏት – የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣስ 10 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከተለያዩ ቋሚ ኮሚቴዎች የተውጣጡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራሮች ከአውሮፓ ህብረት ፓርላማ አባላት ጋር በኢትዮጵያና በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱም በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው የጸጥታና የፖለቲካ ጉዳዮች የምክር ቤቱ…

1 ሺህ 521 የአሸባሪው ሸኔ አባላት የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ሰላማዊ ሕይወት ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጥፋት ተልዕኮ ተቀብለው በኦሮሚያ ክልል ሲንቀሳቀሱ የቆዩ 1 ሺህ 521 የአሸባሪው ሸኔ አባላት ለሁለት ወራት የተሃድሶ ስልጠና በመውሰድ ወደ ሰላማዊ ሕይወት መመለሳቸው ተገለጸ። ለሰልጣኞቹ በቢሻን ጉራቻ ከተማ ቶጋ ካምፕ የቃለ መሐላና…

በኬንያ በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ174 ሰዎች በላይ ሕይወት ተቀጠፈ

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣስ 10 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኬንያ በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ174 በላይ ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡ እንደ ስፑትኒክ ዘገባ የጎርፍ አደጋው የተከሰተው በኤልኒኖ ተፅዕኖ ምክንያት በዘነበ ያልተለመደ የዝናብ መጠን መሆኑ ተመላክቷል፡፡ በቅርቡ የተመዘገበው የሰዎች ኅልፈት…

ቻይና ለኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣስ 10 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቻይና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጋራ መስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ኢ/ር)…