Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ በ3ኛው የቻይና-አፍሪካ የንግድ እና ኢኮኖሚ ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈች ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በ3ኛው ቻይና-አፍሪካ የንግድ እና ኢኮኖሚ ኤክስፖ ላይ እየተሳተፉ ነው፡፡ በቻይና ሁናን እየተካሄደ በሚገኘው ኤክስፖ ላይ የ53 አፍሪካ ሀገራት ተወካዮች እና የበርካታ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች አመራሮች…

አገራዊ እሴቶች ለብሔራዊ መግባባት ያላቸውን አበርክቶ የሚዳስስ መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አገራዊ እሴቶች ለብሔራዊ መግባባትና ለአገር ግንባታ ያላቸውን አበርክቶ የሚዳስስ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡ "አገራዊ እሴቶች ለብሔራዊ መግባባት" በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሄደ የሚገኘው መድረክ÷ በሰላም ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ…

የአርሶ አደር ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ይፋዊ ርክክብ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው እለት 3 ሺህ 451ለሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አርሶ አደሮች የአርሶ አደር ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ይፋዊ ርክክብ በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል። በርክክብ መድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ የከተማዋ ከፍተኛ…

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የሰብዓዊ መብት ጥስት ክስ በማንሳት ምንም የፋይናንስ ድጋፍ ክልከላ እንደማይደረግባት አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የሰብዓዊ መብት ጥስት ክስ በማንሳት ሀገሪቱ ከዚህ በኋላ ምንም አይነት የፋይናንስ ድጋፍና አቅርቦት ክልከላ እንደማይደረግባት አስታወቀች። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሰነድን ዋቢ አድርጎ ፎሬይን ፖሊሲ…

ዐቃቤ ሕግ በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የሽብር ወንጀል ክስ መሰረተ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፍትሕ ሚኒስቴር የተደራጁ እና የድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የሽብር ወንጀል ክስ መስርቷል። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረ-ሽብርና የሕገመንግስት ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በዐቃቤ…

የወረዳ ዋና ስራ አስፈጻሚና ምክትላቸው የመስሪያ ቦታ ለመስጠት ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ዋና ስራ አስፈጻሚና ምክትላቸው በመስሪያ ቦታ አሰጣጥ ተደራድረው የሙስና ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ መያዙን ፖሊስ አስታወቀ። የጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ረ/ኮሚሽነር ፋሲካ ፈንታ…

ሩሲያ ከምዕራባውን ጋር ለመፎካከር ዝግጁ ናት አሉ ፕሬዚዳንት ፑቲን

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ በየትኛውም ዘርፍ ከምዕራባውን ጋር ለመፎካከር ዝግጁ ናት ሲሉ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ተናገሩ፡፡ ፕሬዚዳንት ፑቲን“ለመጪው ጊዜ አዲስ ሃሳብ” በተሰኘ ፎረም ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር÷የምዕራውያን ሀገራት በሩሲያ ላይ የጣሉት…

2ኛው ዙር ሀጫሉ አዋርድ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀጫሉ ፋውንዴሽን አዘጋጅነት የሚካሄደው ሁለተኛው ዙር ሀጫሉ አዋርድ እየተካሄደ ነው። ባለፈው ዓመት በ10 ዘርፎች የተካሄደው አዋርዱ ÷ዘንድሮ በ12 ዘርፎች ነው እየተካሄደ የሚገኘው። ከዘርፎቹ ውስጥ የዓመቱ ምርጥ አልበም፣ ዘፈን፣ አቀናባሪ፣…

በትግራይ ክልል ለሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳቶች የተቀናጀ ምላሽ ለመስጠት ከአጋር አካላት ጋር ምክክር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል ተከስቶ በነበረው ግጭት ምክንያት ለደረሱት የሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳቶች ምላሽ ሰጪ ዕቅድ ተግባራዊ በሚሆኑበት ሁኔታ ላይ ከአጋር አካላት ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሰላም ስምምነቱን መሰረት…

ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል። አቶ ኦርዲን እና ካቢኔያቸው በጉብኝታቸው÷ በ175 ሚሊየን ብር ወጪ እየተገነባ ያለውን ባለ 4 ወለል የእሳት እና ድንገተኛ አደጋ…