Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፊት ለፊት በደረሰ የእሳት አደጋ በስድስት የንግድ ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ…

ሩሲያ “ለወዳጅ” ሀገራት ነዳጅ የምትልክበትን አቅጣጫ ልትቀይር መሆኑን ገለጸች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ “ለወዳጅ” ሀገራት ነዳጅ የምትልክበትን አቅጣጫ ልትቀይር መሆኑን የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ኖቫክ ተናገሩ፡፡ ሩሲያ በዚህ አመት የዘይት እና የነዳጅ ምርቶቿን ወደ “ወዳጅ” ሀገራት ለመላክ እና አጠቃላይ አቅርቦቱንም ከ75…

በጤና ተቋማት ያለው የመድሀኒት አቅርቦት 84 በመቶ ደርሷል ተባለ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 6 ወራት በጤና ተቋማት በየደረጃቸው ያለው የመድሀኒት አቅርቦት 84 በመቶ መድረሱን የጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ሚኒስቴሩ ባቀረበው የ2015 ዓ.ም የ6 ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እንደገለጸው÷ ባለፉት 6 ወራት በግዥና በዓይነት በእርዳታ…

የጅቡቲ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎት እንዳላቸው ገለጹ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጅቡቲ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች  ገብተው መዋዕለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎት እንዳላቸው ገለጹ፡፡ በጅቡቲ የንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የሱፍ ሙሳ ዳዋሌህ የተመራ ልዑካን ቡድን የቂሊንጦ እና ቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን…

ምርጫ ቦርድ እውቅና ለሰጣቸው ታዛቢዎች ጥሪ አቀረበ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የሚያካሂደውን የሕዝበ ውሣኔ ጊዜያዊ ውጤት የማጣራትና የማረጋገጥ ሥራ እንዲታዘቡ እውቅና ለሰጣቸው ታዛቢ አካላት ጥሪ አቀረበ፡፡ ቦርዱ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና…

በመኖሪያ ቤት አቅርቦትና የከተማ መሬት አስተዳደር ሥርዓት ላይ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል ተባለ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በግማሽ ዓመቱ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት እና የከተማ መሬት አስተዳደር ሥርዓት ላይ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በመንግስት፣ ሪል-ስቴት፣ በግል እና በማኅበራት 119…

በጦርነት ምክንያት የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ ለመገንባት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጦርነት ምክንያት የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ ለመገንባት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ የ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ሪፖርቱን አቅርቧል፡፡ በሪፖርቱ…

የአፍሪካ ህብረት አመታዊ ጉባኤ ነገ በስራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 36ኛው የአፍሪካ ህብረት አመታዊ ጉባኤ ነገ በስራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ እንደሚጀምር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ዛሬ በሰጡት መግለጫ÷ በስብሰባው ኢትዮጵያ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና…

የዓለም ባንክ መንግስት ለሚያከናውናቸው የልማት ተግባራት የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚቀጥል አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ ከዓለም ባንክ ልዑካን ቡድን አባላት ጋር ተወያይተዋል፡፡   በውይይታቸውም በጋራ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ተግባራትን በመለየት በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል፡፡  …

ባለፉት ስድስት ወራት 222 ቢሊየን ብር ጠቅላላ ገቢ መገኘቱ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2015 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት 222 ቢሊየን ብር ጠቅላላ ገቢ መገኘቱ ተገለፀ፡፡ በበጀት ዓመቱ 438 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት የታቀደ ሲሆን÷ ባለፉት ስድስት ወራት 222 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱ ተገልጿል፡፡ ያለፈው…