Fana: At a Speed of Life!

የዓለም ባንክ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ባንክ በቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ከዓለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ኦስማኔ ዲዮን ጋር ተወያይተዋል፡፡…

ከ18 ሺህ የትምህርት ማስረጃዎች 900ዎቹ ሐሰተኛ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ18 ሺህ የትምህርት ማስረጃዎች ላይ የሕጋዊነት ማረጋገጫ ተደርጎ 900ዎቹ ሐሰተኛ ሆነው መገኘታቸውን የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን አስታወቀ። የትምህርት ማስረጃዎቹ ተመሳስለው የተሰሩ፣ እውቅና ከሌለው ተቋም የተሰጡ፣ ባልተፈቀደ የሙያ መስክ…

በአማራ ክልል ለሚገኙ ተፈናቃዮች ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን በአማራ ክልል የተፈናቃዮች ቁጥር እየጨመረ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረበ፡፡ የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር እታገኝ አደም ከተለያዩ ክልሎች ተፈናቅለው በክልሉ የሚገኙ ዜጎች…

ፋሲል ከነማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን ረቱ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ፡፡ የፕሪሚየር ሊጉ 17ኛ ሣምንት የጨዋታ መርሐ ግብሮች በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨሲቲ ስታዲየም ተካሂደዋል፡፡ ዐፄዎቹ ከወላይታ ድቻ ጋር…

አቶ ሽመልስ አብዲሳ በኦሮሚያ ክልል ለተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ አመሰገኑ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ዛሬ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ከለውጡ ወዲህ ለተከናወኑ ተግባራት ሰልፍ በመውጣት ድጋፍ ላቀረቡ ወገኖች ምስጋና አቀረቡ፡፡ አቶ ሽመልስ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷…

የምርጥ ዘር እጥረት እንዳያጋጥም እየተሠራ ነው- ግብርና ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለ2015/16 የምርት ዘመን 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል ምርጥ ዘር ለማቅረብ በትኩረት እየሠራ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ ለክልሎች የሚደለድለው ምርጥ ዘር በኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የምርጥ ዘር ድርጅት እና ኮርቴቫ…

የአዲስ አበባ ከተማ ለ500 ሰዎች ማዕድ አጋራ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 1444ኛውን የረመዷን ፆም ምክንያት በማድረግ ዛሬ ለ500 ሰዎች ማዕድ አጋራ፡፡ ለዚሁ መርሐ ግብር አስተዳደሩ ከ6 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ማድረጉ ተገልጿል፡፡ ለእያንዳንዱ አቅመ ደካሞችና አረጋውያን…

አትሌት አበጀ አያና የፓሪስ ማራቶንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት አበጀ አያና ዛሬ የተካሄደውን የፓሪስ ማራቶን አሸነፈ፡፡ አትሌት አበጀ ውድድሩን ያሸነፈው 2 ሰዓት ከ7 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት ነው። ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ጉዬ አዶላ 2 ሰዓት 7 ደቂቃ ከ35 ሰከንድ በመግባት…

የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ በክልሉ ለተደረገው የድጋፍ ሰልፍ ምስጋና አቀረበ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በክልሉ ከለውጡ በኋላ የተገኘውን ድልና ስኬት ለማስቀጠል ለተደረገው የድጋፍ ሰልፍ ምስጋና አቅርቧል፡፡ የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ፈቃዱ ተሰማ÷ ከለውጡ በኋላ የተገኘውን ድልና ስኬት…

ጊዜያዊ ፈተናዎችን ሁሉ ተሻግረን የኢትዮጵያን ብልጽግና እናረጋግጣለን-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጊዜያዊ ፈተናዎችን ሁሉ ተሻግረን የኢትዮጵያን ብልጽግና እና የሕዝቦቿን አንድነት እንደምናረጋግጥ የፀና እምነት አለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ መጋቢት 24…