Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ እና ቤላሩስ በባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ስፖርት ዘርፎች በትብብር ለመሥራት ያለመ ምክክር አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ከቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ሪዚሄንኮቭ ጋር በሁለትዮሽ የሥራ ማዕቀፍ ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ የሁለትዮሽ የሥራ ማዕቀፉ፤ በባህል፣ በስፖርትና በኪነጥበብ ዘርፍ ሀገራቱ በትብብር እንዲሠሩ የሚያስችል…

በትግራይ ክልል ምርታማነትን ለማሳደግ ዘመናዊ አሰራርን መከተል ይገባል –  ሌ/ጄ ታደሰ ወረደ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የግብርና ዘርፍን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል ዘመናዊ አሰራርን መከተል ይገባል ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ሌ/ጄ ታደሰ ወረደ ገለጹ፡፡ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ከባለድርሻ…

በመዲናዋ ለትንሳዔ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር በቅንጅት እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በትንሳዔ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳያጋጥም በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ ገለጹ። የአዲስ አበባ ከተማ የኑሮ ውድነትና ሕገ-ወጥነት መከላከል ግብረ…

በትግራይ ክልል 2ኛው ዙር የሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በትግራይ ክልል በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ 2ኛው ዙር የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ዛሬ በመቐለ ከተማ ተጀምሯል። የፌዴራል መንግስት በመደበው ከ670 ሚሊየን ብር በላይ በጀት ወደ ተግባር የገባው ፕሮግራሙ ከ3 ሺህ…

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል – ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተመዘገበው ስኬት ለሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የ2017 በጀት…

የባህር በር ጉዳይን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እንዲያገኝ ማድረግ ተችሏል – ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተሻለ ተቀባይነት እንዲያገኝ ማድረግ መቻሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የ2017 በጀት ዓመት የሦስተኛው ሩብ…

3ኛው የአፍሪካ ብየዳ ጉባዔ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሶስተኛው የአፍሪካ ብየዳ ፌዴሬሽን ዓመታዊ ጉባዔና ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል፡፡ በጉባዔው የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)፣ የአፍሪካ ብየዳ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት መሐመድ አብደል-አሊም (ፕ/ር) እና ሌሎች…

የብልጽግና ግባችንን ለማሳካት ተቋማት ቀን ከሌት ሊተጉ ይገባል – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀገራዊ የብልጽግና ግባችንን እና ዓመታዊ እቅዶቻችንን ለማሳካት ተቋማት ቀን ከሌት ሊተጉ ይገባል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አሳሰቡ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚና…

ኢትዮጵያና ብራዚል የሰላም እና ደህንነት ትብብራቸውን ለማጠናከር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እና ብራዚል ያላቸውን ታሪካዊ ግንኙነት በሰላም እና ደህንነት ዙሪያ ለማጠናከር የሚያስችል ውይይት ተካሂዷል። በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ከብራዚል የመከላከያ ሚኒስትር ጆዜ ሙሲዮ ሞንቴሮ ፊልሆ ጋር ተወያይተዋል።…

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በ26ኛ መደበኛ ስብሰባው የ2017 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች ዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ እየመከረ ነው። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በስብሰባው በክልሉ…