Fana: At a Speed of Life!

ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሰው ሠራሽ ሐይቅ 753 ቶን የዓሣ ምርት ተገኘ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሰው ሠራሽ ሐይቅ 753 ቶን የዓሣ ምርት መገኘቱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ኢቴቻ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ምርቱ የተገኘው ባለፉት ሰባት ወራት ፈቃድ የወሰዱ አራት ዓሣ አምራች ማኅበራት…

የአልሸባብ የሽብር ቡድን የጋንታና የጦር መሪዎችን ጨምሮ 41 ግለሰቦች እስከ ዕድሜ ልክ በሚደርስ እስራት ተቀጡ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) መቀመጫውን በሶማሊያ ያደረገው የአልሸባብ የሽብር ቡድን የጋንታና የጦር መሪዎችን ጨምሮ 41 ግለሰቦች እስከ ዕድሜ ልክ በሚደርስ ጽኑ እስራት ተቀጡ። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ድሬዳዋ ምድብ 4ኛ ወንጀል ጅግጅጋ ተዘዋዋሪ ችሎት ተከሳሾቹ…

ገርድ ሙለር የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) ዋና ዳይሬክተር ገርድ ሙለር እና ልዑካን ቡድናቸው የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል።   ዋና ዳይሬክተሩ የዓድዋ ድል መታሰቢያ በውስጡ የትናንት ታሪክን ብቻ ሳይሆን…

ተመድ የአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ እንዲያገኙ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ እንዲያገኙ አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርጋለን ሲሉ የተባበሩት መንግስታቱ ድርጅት ዋና ፀሃፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሃና ሰርዋ ገለጹ። ሃና ሰርዋ አፍሪካ የሚያጋጥሟትን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች…

የዘመናዊውን ቅኝ ግዛት ስርአት የሚቃወሙ ሀገራት ፎረም ምስረታ ስብሰባ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሩሲያው ገዥ ፓርቲ "ዩናይትድ ራሺያ ፓርቲ" አዘጋጅነት የዘመናዊውን ቅኝ ግዛት ስርአት የሚቃወሙ ሀገራት ፎረም ምስረታ ስብሰባ ከፈረንጆቹ የካቲት 15 እስከ 17 ቀን 2024 በሞስኮ ከተማ ተካሂዷል። መርሀ ግብሩ ላይ በብልጽግና…

የኤችአይቪ/ኤድስ ስርጭትን ለመቆጣጠር አስገዳጅ መመሪያ በት/ቤቶች ተግባራዊ ሊደረግ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኤችአይቪ/ኤድስ ስርጭትን ለመቆጣጠር አስገዳጅ መመሪያ በትምህርት ቤቶች ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በሚኒስቴሩ የኤችአይቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ጽህፈት ቤት መሪ ስራ አስፈጻሚ ፈቃዱ ያደታ ለፋና ብሮድካስቲንግ…

የጉጂ ኦሮሞ አባ ገዳ ስልጣን ርክክብ ለማካሄድ የተለያዩ ስነ-ስርዓቶች እየተከናወኑ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዚህ ሳምንት በመጪው ረቡዕ ለሚካሄደው የጉጂ ኦሮሞ አባ ገዳ ስልጣን ርክክብ በሜኤ ቦኮ የተለያዩ ስነስርዓቶች እየተከናወኑ ነው፡፡ ከገዳ ሀርሙፋ ወደ ገዳ ሮበሌ ለሚደረገው ሽግግር ነው አባ ገዳዎች በአርዳ ጂላ ሜኤ ቦኮ ከትመው ስነ ስርዓቶችን …

ጨፌ ኦሮሚያ የአቶ ታዬ ደንዳአን ያለመከሰስ መብት አነሳ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጨፌ ኦሮሚያ እያካሄደ ባለው 6ኛ የሥራ ዘመን 3ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ጉባዔ የአቶ ታዬ ደንዳአን ያለመከሰስ መብት አንስቷል፡፡ የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ የነበሩት ታዬ ደንደአ ታኅሣስ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ከሽብር ድርጊት ጋር…

የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በስኬት መጠናቀቁን ግብረ-ኃይሉ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እና 44ኛው የአስፈፃሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ በስኬት መጠናቀቁን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታውቋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማን ሰላምና ደህንነት የበለጠ ለማጠናከር፣ የትራፊክ ፍሰቱን…

የሀሪ ኬን የዋንጫ እርግማን

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቶተንሃም እና የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን የምንጊዜም ጎል አስቆጣሪው ሃሪ ኬን ከአዲሱ ትውልድ ምርጥ አጥቂዎች ውስጥ ስሙ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ በእግር ኳስ ሜዳ ላይ የጎላ አስተዋጽኦ ቢያደርግም ዋንጫ አንስቶ በመሳም ረገድ ግን ዕድል ከእሱ ጋር…