Fana: At a Speed of Life!

የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን በይበልጥ ማሳደግ ይገባል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቱሪዝም ዘርፍን ለማነቃቃት እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች አበረታች በመሆናቸው በይበልጥ ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ምሁራን ተናገሩ፡፡ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ለጋራ ትርክት ግንባታ ከፍተኛ ድርሻ ስላለው ዘርፉን በይበልጥ ለማልማት መትጋት እንደሚገባ…

ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የእምነት ተቋማት ሚና እንዲያጠናክሩ ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፍሪካ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ የእምነት ተቋማት ያላቸውን ሚና አጠናክረው እንዲቀጥሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ አስገነዘቡ፡፡ 3ኛው ዓለም አቀፍ የሰላም፣ የአብሮነትና የልማት ጉባዔ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። ፕሬዚዳንት ታዬ…

ቀጣናዊ ደኅንነትን ለማስጠበቅ የጸጥታ ተቋማትን ማጠናከር አስፈላጊ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በምስራቅ አፍሪካ ያለውን ቀጣናዊ ደኅንነት ለማስጠበቅ ቀጣናዊ የጸጥታ ተቋማትን ማጠናከር እና በትብብር መስራት አስፈላጊ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ፡፡ የአፍሪካ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ኮሚቴ የምስራቅ አፍሪካ…

የበልግ ወቅት የመጨረሻ ወር የዝናብ ስርጭትን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሚዋዥቅ እና ተለዋዋጭ እየሆነ የመጣውን የበልግ ወቅት የመጨረሻ ጊዜያት የዝናብ ስርጭት በአግባቡ በመሰብሰብ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል። በኢንስቲትዩቱ የትንበያ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር…

ምክር ቤቱ አራት ስምምነቶችን አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 29ኛ መደበኛ ስብሰባው አራት የስምምነት አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል። በቀዳሚነት የጸደቀው ለአካባቢ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት በኢትዮጵያ እና በጣሊያን መንግስት መካከል…

3ኛው ዓለም አቀፍ የሰላም፣ የአብሮነትና የልማት ጉባኤ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ እና ነገ በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄደው 3ኛው ዓለም አቀፍ የሰላም፣ የአብሮነትና የልማት ጉባኤ መካሄድ ጀመረ። ጉባኤው በዋናነት የአፍሪካ የእምነት ማህበረሰብ ዘላቂ የልማት ግቦች ስኬትን ማፋጠን፣ የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ለማሳካት…

የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲው የዘርፉን አስተዋፅኦ ለማሳደግ ያስችላል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ የዘርፉን አስተዋፅኦ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑ ተገለጸ። ለሐረሪ ክልልና ድሬዳዋ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ማስተዋወቂያ መድረክ በሐረር ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ…

የኮንፈረንስ ቱሪዝም የስበት ማዕከል እየሆነች ያለችው ኢትዮጵያ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የኮንፈረንስ ቱሪዝም የስበት ማዕከል እየሆነች ነው ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴዔታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ በዘርፉ የፖሊሲ ለውጥ መደረጉን ጨምሮ ኮሪደር ልማትና ሌሎች ምቹ መሠረተ-ልማቶች፣ ከቪዛ ጋር ተያይዞ የተደረጉ ማሻሻያዎች…

ኢትዮጵያ የቀጣናውን ሰላም ለማስጠበቅ የሚያስችል ሪፎርም እያደረገች መሆኗ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከሀገር ባለፈ የቀጣናውን ሰላም እና ደኅንነት ለማስጠበቅ በሚያስችል መልኩ ተቋማዊ ሪፎርም እያደረገች መሆኗን የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ጀኔራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ተናገሩ። አምባሳደር ሬድዋን ይህን…

የኢትዮ ኮደሮች ስልጠና ያጠናቀቁ ከ270 ሺህ በላይ ወጣቶች የምስክር ወረቀት ወስደዋል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደሮች ፕሮግራም እስከ አሁን ከ270 ሺህ የሚልቁ ወጣቶች ሥልጠናቸውን በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት መውሰዳቸው ተገለጸ፡፡ በመላ ሀገሪቱ ባለፉት 10 ወራት ከ800 ሺህ በላይ ወጣቶች ተመዝግበው ስልጠናቸውን በመከታተል ላይ…