Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ድሮን ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ገንብታለች- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ድሮን አምርቶ ከመጠቀም ባሻገር ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም መገንባቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሲቪልና ወታደራዊ አገልግሎት የሚውሉ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን (ድሮን)…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የስካይ ዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪን መረቁ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የስካይ ዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪን መረቁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት በሀገር ውስጥ ድሮን ስለማምረት ማሰብ የማይታሰብ ነበር ብለዋል፡፡…

ቻይና የኢትዮጵያ የምንጊዜም የልማት አጋር ናት- አምባሳደር ተፈራ ደርበው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ቻይና የኢትዮጵያ የምንጊዜም የልማት አጋር ናት ሲሉ በቤጂንግ የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ገለፁ፡፡ የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት በጋራ ተጠቃሚነት እና እድገት መርህ ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ነው አምባሳደሩ ያረጋገጡት፡፡ ሀገራቱ…

 በሶማሌ ክልል የፖለቲካ ምኅዳሩን ለማስፋት በተሰጠው ትኩረት ከፍተኛ መሻሻል መምጣቱ ተገለጸ

አዲስ አበባ፤ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሶማሌ ክልል የፖለቲካ ምኅዳሩን ለማስፋት በተሰጠው ትኩረት ከፍተኛ መሻሻል መምጣቱን የሶማሌ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ መሀመድ ሻሌ (ኢ/ር) ገለጹ። በክልሉ አስተማማኝ ሰላም ከማስፈን ባሻገር የፖለቲካ ምኅዳሩን ለማስፋት…

የወንጀል ቅጣት አወሳሰን ረቂቅ መመሪያ ለተመሳሳይ ወንጀሎች ተቀራራቢ ውሳኔ ማሳለፍ ያስችላል ተባለ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በወንጀል ቅጣት አወሳሰን ላይ የተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተመሳሳይ ወንጀሎች ተቀራራቢ ውሳኔ ማሳለፍ የሚያስችል መሆኑን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ። በተሻሻለው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን ረቂቅ መመሪያ ላይ የቅጣት…

ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን በኢትዮጵያ ለ49ኛ ጊዜ ተከበረ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለም አቀፉ ሴቶች ቀን በኢትዮጵያ ደረጃ ለ49ኛ ጊዜ ተከብሮ ውሏል፡፡ ቀኑ በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች እና ከተሞች በተለያዩ ዝግጅቶች፤ ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል በሚል መሪ ሐሳብ ተከብሯል፡፡

ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በነጋሶ ጊዳዳ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ተማሪዎችን አበረታቱ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በደምቢዶሎ ከተማ ነጋሶ ጊዳዳ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ተማሪዎችን አበረታቱ፡፡ በዚሁ ጊዜ፤ ተማሪዎች ኩረጃና ስርቆት የሚጠየፉ፣ በራሳቸው የሚሠሩና ጊዜያቸውን በአግባቡ የሚጠቀሙ…

የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ በ7 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ካቢኔ ባካሄደው 4ኛ ዓመት 8ኛ መደበኛ ስብሰባ በሰባት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ በዚሁ መሠረት አንደኛ፤ ሀገራዊ እና ማኅበራዊ ፋይዳ ላላቸው የማኑፋክቸሪንግ እና ሌሎች ፕሮጀክቶች የሚውል የቦታ…

የተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች የታሪክ እጥፋት የሚያመጡ ናቸው – አቶ አደም ፋራህ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከተረጂነት በመላቀቅ የተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች የታሪክ እጥፋት የሚያመጡ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። ብልጽግና ፓርቲ ለሦስት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን የሥድስት ወራት የስራ…

የሩዝ ምርትን በሕገ ወጥ መንገድ ሽጠው ለግል ጥቅም አውለዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች ተከሰሱ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለማሕበረሰቡ በቅናሽ እንዲሸጥ የቀረበ የሩዝ ምርትን በሕገ ወጥ መንገድ ሽጠው ለግል ጥቅም በማዋል ሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት ተከሰሱ። የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ትናንት ከሠዓት በኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን…