Fana: At a Speed of Life!

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 5 ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር አምስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ዛሬ ከሚደረጉ ጨዋታዎች መካከል ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ አስቶንቪላ በሜዳው ቪላ ፓርክ ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል። በ54…

በዓሉን ስናከብር የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመርዳት ሊሆን ይገባል – ጉባኤው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓሉን ስናከብር የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመርዳት እና በመጠየቅ ሊሆን ይገባል ሲል የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አስገነዘበ። ጉባኤው የትንሣኤ በዓልን አስመልክቶ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳቹህ መልዕክት…

ስቅለት ፍቅር፣ ይቅር ባይነትና ትሕትና በተግባር የተገለጠበት ዕለት ነው – የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት አስተምህሮ ፍቅር፣ ይቅር ባይነትና ትሕትናን በተግባር የተገለጠበት ዕለት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶች ገለፁ። የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ…

በድሬዳዋ የእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች ከስግደት ለሚመለሱ ክርስቲያን ምዕመናን ማዕድ አጋሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በድሬዳዋ የእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች ከስግደት ለሚመለሱ የክርስትና እህት ወንድሞቻቸው ማዕድ አጋርተዋል። የስቅለት በዓል ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ በድሬዳዋ በሚገኙ የክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች ዘንድ በስግደት፣ በዝማሬ፣ በፀሎት እና በንስሃ ታስቦ…

በባሕር ዳር ከተማ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች የበዓል መዋያ ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በባሕር ዳር ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ለ461 ወገኖች ለትንሳዔ በዓል መዋያ ዛሬ ድጋፍ ተደርጓል። ድጋፉ የተደረገው ከተማ አስተዳደሩ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር ባሰባሰበው ከ18 ሚሊየን 300 ሺህ ብር በላይ እንደሆነ በርክክቡ…

ከስቅለቱ የምንማረው ይቅርታ ማድረግን፣ ትህትናንና መከባበርን ነው – ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት የምንማረው የሰው ልጆች እርስ በርሳቸው ይቅርታ ማድረግን፣ ትህትናን እና መከባበርን ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል ገለጹ። የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት…

ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን አቻቸው ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) አዲስ ከተሾሙት የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር መንዳይ ሰማያ ኩምባ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በተለያዩ ትኩረት በሚሹ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡…

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የቬይትናም ቆይታ ስኬታማና የኢትዮጵያን አስፈላጊ አጋርነት ያረጋገጠ ነው – ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቬይትናም የነበራቸው ጉብኝት ስኬታማና የኢትዮጵያን አስፈላጊ አጋርነት ያረጋገጠ ነው ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው…

 በበዓል ወቅት በዲጂታል ክፍያ ስንፈጽም ልንተገብራቸው የሚገቡ ጥንቃቄዎች፡-

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በበዓላት ወቅት ሸማቾች በዲጂታል ምህዳሩ ውስጥ ግብይቶችን ሲፈጽሙ ለከፍተኛ መጭበርበር ሊጋለጡ ይችላሉ። ምክንያቱም አጭበርባሪዎች ይህ ወቅት ከፍተኛ ግብይት የሚፈጸምበትና ሸማቾች ሃሳባቸው በበዓል ጉዳዮች እንደሚጠመድ ስለሚያውቁ የተለያዩ…

ነገሌ አርሲ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አደገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ለ እየተሳተፈ የሚገኘው ነገሌ አርሲ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል። ዛሬ የምድብ 21ኛ ጨዋታውን ያደረገው ነገሌ አርሲ ስልጤ ወራቤን 3 ለ 0 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎም ክለቡ አንድ ጨዋታ…